ዘመድኩን በቀለ


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Siyosat


የዘመድኩን በቀለ ጦሟሩን እንደወረደ የሚለቀቅበት ስለሆነ ሁላችሁም ዘመዴን አድናቂዎች ተቀላቀሉት ጆይን አድርጉት ሸሩን ትታችሁ ሼር አድርጉት

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Siyosat
Statistika
Postlar filtri


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
"…በሉማ ወደ ከተማዬ፣ ወደ ምሽጌ የምትወስደኝን ባቡር ልያዝ። ባቡር ውስጥ ሆኜ እቤቴ እስክደርስ ነው በአስተያየት መስጫ ሰንዱቁ ውስጥ የዶላችሁልኝ አስተያየት ለቅሜ ተራ በተራ የማነው። እግረ መንገዴንም ብሎክ ባን የሚባለውን ወገብ ዛላ መቁረጫ የቴሌግራም ሰይፌን ይዤ ባለጌ፣ ስድአደግ፣ ቆሻሻ ኮመንቱን የወዘፈ ውዝፍ ከገኘው እየቀሰፍኩ ነው ቤቴን፣ መንደሬን እያጸዳሁ የምሄደው።

"…ነገ መንገደኛ ነኝ። ከጎዶኞቼ ጋር አውሮጳ ጎረቤት ሀገር ደረስ ብዬ ነው የምመጣ። የጠዋቱ ምስጋና አይቀርም። አይቋረጥም። 1ሺ ሰው ከሞላ በኋላ ግን ቤቴ ይዘጋል። በምሄድበት ሃገር ነፃ ጊዜ ካገኘሁ ከጮቄ ተራራ ሆኜ ሸገርን እያየሁ አንድ ሁለት ልለቅባችሁ እሞክራለሁ።

• እናንተም አደራ ባለጌ ካያችሁ 👉🏿 Block ዘመዴ እያላችሁ በመጠቆም ተባበሩኝ።

• ሻሎም…! ሰላም…!


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
መልካም…

"…ይሄን 22 ሺ ሰው አንብቦት 49 ፍሬ ሰዎች ጓ 😡 ብው የሉበትንና ነገ ማክሰኞ ባለመኖሬ ምክንያት በተለዋጭ በዛሬ በእረፍት ቀኔ በነገ ምትክ የቀረበውን ልዩ የድርድርና የግርግር፣ የፉገራም፣ አጀንዳ ማስቀየሪያም ጭምር ነው ብዬ በመገንዘብ በእኔ በማይሙ፣ በመራታው በጃል ቆቱ ወዲ አስገዶም አሸበርቲው፣ አስነቀልቲው ዘመዴ ተዘጋጅቶ የቀረበውን ርእሰ አንቀጽ በእናንተ ያነሰ ካለ ወደ ምትጨምሩበት፣ የበዛ፣ የተጋነነ ነገር ካለ ደግሞ ወደምትቀንሱበት፣ የእናንተም ሓሳብ ወደሚደመጥበት መርሀ ግብራችን እነናመራለን።

"…በሬ ክፍት ነው። በጨዋ ደንብ ተቃውሞ ሓሳብ መስጠት ይቻላል። ክልክሉ ነገር የመንደሬን ሰው ዓይን የሚያቆሽሽ ቀፋፊ ስድብ ብቻ ነው። ላለመቀሰፍ ራሳችሁን ተቆጣጥራችሁ ጮጋ ለማለት ሞክሩ። ካላስቻላችሁ እንግዲህ ምን አደርጋለፍ በብሎክ ሰይፌ ቀስፌ ወገብ ዛላህን ቆምጬ እገላግልህሃለሁ።

"…ጻፉ፣ ተንፍሱ፣ በጨዋ ደንብ ተወያዩ። ይሄ የእኔ ፔጅ ነው። የእኔን የውስጥ ሓሳቤንና እኔን የመሰሉ አንዳንድ መተርጉማን ወዳጆቼ ሓሳብ የሚንሸራሸርበት ፔጄ ነው። ከደበርኩህ ውልቅ ትላታለህ እንጂ በፔጄ ላይ እንድትጸዳዳ አልፈቅድልህም። ከደበርኩህ ንካው።

"…ዘመዴ አክሊለ ገብርኤል ነኝ ከጮቄ ተራራ… 😂😂 …✍✍✍


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
👆⑤ ✍✍✍ …እስኬው ከአቢይ አሕመድ ከኦነግ ኦሮሙማው ጋር ተደራድሮ የኦነግ ኦሮሙማው ጦር ከዐማራ ክልል እንዲወጣ ካደረጉለት ለአብይም ለእንሽላሊትም ትልቅ ድል ነው የሚሆነው። አስቡበት።

1ኛ. አብይ ከመሬት ተነሥቶ የዛለና የተሰላቸ ጦሩን ከክልሉ ቢያወጣ ሽንፈቱን እንዳመነ ይቆጠርበታል። እንደ ፌስታል ዓይነቱን ወስላታ ተጠቅሞ በድርድር ሰበብ ከሞት የተረፈውን ወታደሩን ካወጣም ሽንፈቱን ወደ ድል ቀየረ ማለት ነው። ሁሌም እንደሚያደርገው ነው የሚያደርገው። ከትግራይ ጦሩን በድርድር ስም አወጣ ከዚያስ ለእነ ጌታቸውረዳ እያገዘ እነ ደብረ ጽዮንን እያጠዛጠዘ ዛሬ ይኸው መቀሌን በሸሻ፣ በሻሻን ደግሞ ሮማ መቀሌ አስመስሏት ቁጭ ነው ያለው። አቢይ ዐማራንም ዱቄት አድርጎ ጅማን ፓሪስ ሮም ነው እያስመሰላት ያለው። ፍጠኑ።

2ኛ. አጅሬ እስክድር ነጋ "ይኸው ተደራድሬ ኦነግን ከዐማራ ክልል አስወጣሁት" ካለ፤ በጦርነት ሲኦል ውስጥ የነበረው የዐማራ ሕዝብ ሞት ስለሚቆምለት፣ ትራንስፖርት ትምህርት ጤና ማግኘት ይጀምራል። በዚህም ያለምንም ማወላወል ፌስታልን ለማመስገን ይገደዳል። ያመሰገነዋልም። እፎይ አሳረፈን ይለዋል። በግብር የተማረረው፣ በፋኖም በኦሮሙማውም ጭካኔ የተማረረው ዐማራ ከሚያውቁት መልአክ የማያውቁት ሰይጣን እስክንድርን ያመሰግናል። እሱን ለማወቅ፣ ለማዬትም ይመኛል። ከእስክንድር ውጭ ያለው እውነተኛው ፋኖ ተቀባይነቱ እየቀነሰ ይመጣል። ይሄን ከአሁን ጀምረውታል። ይሄ እንዳይፈጠር ከተፈለገ ፍጠኑ። ጎጃምም፣ ጎንደርም፣ ወሎም፣ እንደ ሸዋ ተሃድሶ፣ ግምገማ፣ ራስን ወደ መመልከት፣ የራቁትን ሕዝብ ወደ ማቅረብ፣ የበደሉትን፣ ያሳዘኑትን፣ ያስከፉትን፣ ያስቀየሙትን፣ ያስኮረፉትን ሕዝብ በፍጥነት መካስ፣ ወንጀለኛ ፋኖ ጨሰዳቢዎችን ሕጋዊና ተገቢ ቅጣት በመቅጣት ብትንቀሳቀሱ መልካም ነው እላለሁ።

"…እነ እስክንድር በኔ ግምት ከአሜሪካ ጋር ነው የሚሰሩት። አሜሪካ ደግሞ ኢትዮጵያን በዓለም ላይ ድራሻቸው ከሚጠፉ አስር አገሮች በሦስተኛ ደረጃ ከ ሶሪያ እና አፍጋኒስታን ቀጥሎ አስቀምጣት ልታጠፋት ያቀደች አገር ናት የሚሉም መተርጉማንም አሉ። ለዚህም ኢትዮጵያን በነ አቢይ እንድትጠፋ ህውሓትን ገልብጣ ብትመጣም እነ አቢይ በሚፈለገው ልክ ሰዉን አልጨፈጨፉም የሚሉም አሉ። እስከአሁን ከጨፈጨፉት በላይ ይጨፈጭፋሉ ተብሎ ቢጠበቅም ጭራሽ ቁጥሩ እየጨመረ ነው የመጣው የኢትዮጵያ ሕዝብ። በተጨማሪ እነ አቢይ የሄዱበት መንገድ ሁሉንም ክልል ሰበብ እየፈለግን ጦርነት እየከፈትን አድቅቀን፣ አውድመን የእኛንም፣ የአሜሪካንንም ፍላጎት እናሳካለን ብለው የያዙት መንገድ ትግራይን አድቅቀው ወደ ዐማራ ሲመጡ እንዳሰቡት አልሆነላቸውም። ትግራይን በፋኖ፣ በኤርትራ ጦር፣ በክልል ልዩ ኃይልና በኦሮሚያ ልዩ ኃይል በሻሻ አድርገው ወደ ዐማራ ሲመጡ አልተሳካላቸውም። በዐማራ ፋኖ ጉሮሮ ማንቁርታቸውን ተያዙ። ተመከቱ። ሂደታቸዉ እንከን ገጥሞት ያሰቡት አልሆን አለ።

"…ስለዚህ አሁን አሜሪካ ከነ አቢይ አሕመድ የተሻለ ኢትዮጵያን አብሶ ዐማራውን እና ኦርቶዶክሱን ያለ ርህራሄ የሚያጠፋላት ቡድን እየፈለገች ነው የሚሉም አሉ። ትራምፕም መጣ ጆ ባይደን የአሜሪካ የውጭ ፖሊስ እምብዛም ብዙ ለውጥ አይደረግበትም የሚሉም አሉ። እናም እነ አማሪካ የነ ጀዋርን ኦነግ ወይም ትግሬ መሩን ኦነግ ሸኔ ወደፊት ማምጣት ሳይፈልጉ አልቀረም። ስለዚህ እነርሱን ወደፊት ለማምጣት እየሄደችበት ያለችውን መንገድ መጀመሪያ ማስተካከል ይኖርባታል ነው የሚሉት ነገርየው ገብቶናል የሚሉ አንዳንድ ግለሰቦች። መጀመሪያ ኢትዮጵያ ውስጥ የታጠቀውን ኃይል በተለይ ዐማራውን በድርድር ስም ትጥቁን ማሰወረድ። ምክንያቱም እነ ሸኔ አቢይን እንዲገለብጡ ብታደርግም አጅሬ ዐማራ የዐማራ ፋኖ መሳሪያው በእጁ ካለ መልሶ ኦነግ ሸኔ ሥራውን እንዳይሠራ አድርጎ ድራሽ አባቱን አጥፍቶ ይገለብጠዋል ስለዚህ ፋኖን በእነ እስክንድር በኩል እንዲደራደር እና ትጥቅ እንዲፈታ ካደረጉት በኋላ ወያኔ በ1983 ዓም ኦነግን መሳሪያውን አስወርዳ እንደ በግ ወደ ካምፕ ነድታ አፍር ከደቼ እንዳበላቸው አሁንም ፋኖን በዚያው መንገድ ሽባ ለማድረግ ነው ሙከራው ነው የሚሉት።

"…ለዚሁም እነ ኢጋድን፣ ኢጋድ ማለት ትግሬው ወርቅነህ ገበዮ ኪዳኔ እና ኦነጉ ኃይሉ ጎንፋ የሚመራው ድርጅት ማለት ነው። እናም በዚያ እንዲመራ፣ እነ የአፍሪካ ኅብረት፣ የአውሮጳ ኅበረት እና ወዘተረፈዎችን ይዛ ድርድር ጀመረች ማለት ነው።  የታጠቀው ኃይል ሸኔ አዲስ አበባ ዙሪያ፣ ሱሉልታና ሰበታ፣ ዝቋላና አቃቂ ሰፍሮ ሳለ ጮቄ ተራራ ላይ ያለው ፋኖ ትጥቅ ይፍታ፣ ካምፕ ይግባ ሲባል ፈጣሪ የመልክታችሁ። ለዚሁም ለጃዋር ብዙ ምልክቶች እየታዩ ነው። ጃዋር መጸሐፍ በመጻፍ በቢቢሲ ጭምር እየታገዘ ወደ ፊት እንዲመጣ የተደረገው፣ የባለፈው ሳምንት በሕዝብ ተወካዮች ፊት ተናገረውና እኛ መሞትም፣ መግደልም መሮናል ስለዚህ ችግራችሁን እናንተ ፖለቲከኞች ተነጋገሩና ፍቱ ብሎ የኦሮሞው ጀነራል እና ጄነራሮልች በቴሌቭዥን መስኮት እንዲያውቁት የተደረገው ምንአልባትም የሆነ ቀን ከመኝታችን ስንነሣ በጥቅሴ የአቢይን አገዛዝ ይገለብጡና፣ የሕዝቡን ትኩሳት ለማብረድ የሚገደለውን ገድለው፣ የሚታሰረውን አስረው ያበቁና፣ ከዚያ መጀመሪያ ካምፕ የገባውን ፋኖ ጨርሰው፣ ቆርጥመው በልተው ሲያበቁ ቀጥሎ በኢትዮጵያ ዐማራውን እና ኦርቶዶክሱን ከሩዋንዳ በሚያስንቅ የዘር ጭፍጨፋ ፈጽመውበት ይጨርሱታል። ቤተ ክርስቲያንንም ያነዷታል። ስለዚህ መታወቅ ያለበት ነገር እነ እስክንድር ነጋ ዐማራውን እንዲያዳክሙ፣ እንዲያበጣብጡ፣ ፋኖውን አስር ትናንሽ ቦታ እንዲከፋፍሉ የአሜሪካ እና የጽንፈኛ ኦሮሞዎች ቅጥረኛ ናቸው ብለው ግግም ይላሉ እነዚህ አንዳንድ መተርጉማኖች። ወያኔም የውስጥ ትኩሳታን ለማስታገስ በወልቃይት በኩል መከሰቷ አይቀሬ ሊሆን ይችላል። የአቶ ገዱም ሁኔታ መጨረሻውም፣ መጀመሪያውም ስላልታወቀ አስተያየት ለመስጠት አስቸጋሪ ነው። የሆነው ሆኖ ዐማራው ፈጣሪውን ተማጽኖ እንደ ጌዴዎን ሰልፉን መቀጠል ብቻ ነው ያለው አማራጭ። ይሄን አለ ብላችሁ ደግሞ ስደቡኝ አሏችሁ። አዝማሪ ሁላ ሰደበኝ አልሰደበኝ እኔ እንደሁ ኬሬዳሽ ነኝ። ኬሬዳሽ።

• ድል ለዐማራ ፋኖ…!
• ድል ለተገፋው ለዐማራ ሕዝብ…!

~ • ይደፈርሳል… ግን ደግሞ ይጠራል…✊

•••

ሻሎም…!  ሰላም…!

ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
አሸበርቲው/አስነቀልቲው
ጥር 19/2017 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ።


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
👆④ ✍✍✍ …እነዚህ ገንዘብ አልደረሳቸውም ተብለው ሁለት አደረጃጀት ተብለው የተጠቀሱት ብቅቱ ነበሩ ወይ? አደረጃጀቶቹስ ተፈጥረዋል ወይ? ሴራ ስታስቡ እኮ የሚያሳምን ብታደርጉት መልካም ነበር። የዛሬ አራት ዓመት ሸዋ ላይ መከታውና ጋሽ አሰግድ እኮ እስክንድር እስኪለያያቸው አንድ ላይ እኮ ነበሩ እኮ። ወሎም ምሥራቅ ዐማራ አንድ ነበር። ጎንደርም ብዙ ነበሩ። የከሸፋችሁ 😂

"…በመጨረሻ ምናላቸው እና አቶ ተፈራ ዘመነ ካሤን እንድትከሱት የላካችሁን አስረስ መዓረይን በቀሽም ድራማችሁ መልሳችሁ ራሱን አስበልታችሁታል። በዘመነ ካሤ ላይ በሚሴረው ሴራም ላይ ተሳታፊነታችሁንም በግልፅ አረጋግጣችኋል። መግቢያው ላይ የተጠየቁትን ጥያቄዎች የመለሰና ማገናዘብ የቻለ ሰው በምናላቸውና በተፈራ የደደብ ቃለምልልስ ዘመነን ለመክሰስ በቂ ዝግጅት አለማድረጋቸውን በቀላሉ መረዳት ይቻላል። እኔ በበኩሌ ለአርበኛ ዘመነ ካሤ እየተከራከርኩለት፣ እየተሟገትኩለትም አይደለም። ዘመነ ራሱ ለራሱ በቂ ከበቂም በላይ ነው። እኔ ጠቤ፣ ሙግቴ ከሴራው ላይ ብቻ ነው። እንዲህ ዓይነት ሴራ በአስረስ መዓረይ ላይ ቢደረግ እንኳ ለአስረስ መዓረይ በዚሁ ልክ ነው የምሟገተው። ሁለቱንም በስልክ ሲደውሉልኝ እንጂ የማውቃቸው በአካል እኮ አላውቃቸውም። ይሄን የማያውቅ ገተት ጎጃም አሰዳቢ አገው ሸኔ ምንም ሳይገባው እኔ ላይ አፉን ሲከፍት ቢነደኝም ግን ማሸነፌን ሳውቅ ደግሞ ኩራት ቢጤ እንደ ሙቀት ያለ ነገርም ይሰማኝና ንዴቴን እረሳዋለሁ። እንዴት ሰው አይባንንም ግን?

"…አሁን እነ እስክንደር እና እነ ጌታ አስራደ በመዓረይ በኩል በዝናቡና በዘመነ ላይ የወጠኑት ክፉ ሴራ ለጊዜውም ቢሆን ሰው ስላወቀው ከሽፎባቸዋል ልንል እንችላለን። ሸንጎና እስኳድ ጎጃምንና ጎንደርን የማዋጋት ጨርሰውት የነበረውም ዕቅድ ፕላኑም ቢሆን በብዙ ፐርሰንት ከሽፏል ልንልም እንችል ይሆናል። ከጎጃም በተከታታይ እንደ ክረምት ዝናብ ይዘንብ የነበረው አደናባሪው፣ አጨናባሪው፣ የዶላር መልቀሚያው የፌክ ሰበር ዜናውም ቢሆን አሁን ቀርቷል። አስረስ መዓረይ የቀረለት ነገር ቢኖር እስከመጨረሻው የሚዋደቅለት ብልፅግና ብአዴንና የሸንጎ የሳይበር ሠራዊቱ ብቻ ናቸው። አልማዝ ባለጭራዋም ከመደንገጧ የተነሣ የቲክቶክ ፊልተር ሳትጠቀም ጋሽ ቾምቤን መስላ ታይታ ደንግጣ የምትሆነውን ነው ያሳጣት። መጀመሪያ አካባቢ በእኔ በዘመዴ ጎጃም መግባት ደንግጦ የነበረው የጎጃም ሕዝብም አሁን መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር እያዛመደ በኃይለኛው ተረጋግቷል። ነገሩ፣ ሴራው ሁሉም ገብቶታል ማለት ይቻላል። እኔ ዘመዴ ከመረጃ ቴቪ ራሴን ያወረድኩበት፣ የእነ ግርማ ከሳ፣ የጎጃም፣ የደቡብ ጎንደር የፋፍዴን፣ የመከታው ፋኖም ፓስተሮች ገመናም ከነ ሴራው ለሁሉም ሰው ተጋልጧል። ይሄ አሪፉ ነገር ነው።

"…እስክንድር ነጋ አሁን ሥራውን ጨርሷል። ተልእኮውን በሚገባ ጨርሷል። ወሎን ሁለት ቦታ፣ ሸዋን ሁለት ቦታ፣ ጎጃምን ሦስት ቦታ፣ ጎንደርን ሦስት ቦታ ከፋፍሎ የነበረ ቢሆንም ጎጃም ሁለቱን አብርሮ አንድ ሆኖ አሸንፎ ነበር። እነ መዓረይ አጀዘቡት እንጂ። ጎንደር ከሦስት ወደ ሁለት መጥተዋል። የሚቀረው የእስክንድርና የአቶ ይርጋ በላይ የደቡብ ጎንደር ፋኖ ነው። ሸዋም ብዙ ንግግር አለ። እነ ጌታ አስራደም የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሰጣቸውን ተልእኮ ጨርሰዋል። አጠናቃዋልም። የሚገደለው ጀግና ጀግና ፋኖ ተገድሎ፣ እንደ አሰግድ ዓይነቱም ታፍኖ የደረሰበት እንዳይታወቅ ተደርጎ፣ እንደ አስረስ ዓይነቱ ጎጃምን ሽባ አድርጎ የቀራቸው እጅ መስጠት ብቻ ሆኖ፣ በድርድሩ ስም ጃልሰኚን መሆን ብቻ ነው የቀረው እንጂ ሥራውን ለብልፅግና ጨርሷል። ጎንደር፣ ወሎና ሸዋ ይሄን ሴራ አስቀድመው ስለነቁ ወጥረው አንድነታቸውን አጥብቀው መያዛቸው እስክንድርን ጫካ ሊያቆየው አይችልም።

"…አስረስ መዓረይም ቢሆን በመጨረሻ ጭራውን ቆልፎ አንገቱን ደፍቶ አደብ ገዝቶ ጮቄ ተራራ ላይ ተቀምጧል። እስክንድርን ተቃውመው ለሎቹ እንደ ድርጅት መግለጫ አውጥተው ሳለ እሱ ብቻውን ዐዋጅ፣ መመሪያና ደንብ ጥሶ ድርድሩን በተመለከተ ጀግና ጀግና እንዲጫወት፣ ከዚያ ግማሽ ደርዘን በሚሞሉ ተከፋይ አክቲቪስቶቹ በኩል ስለራሱ ዋይዋይ ማስባሉ፣ አልማዝ ባለጭራዋም "የአስረስን ፕሮፋይል ፒክቸር እንቀይርለት" በማለት ስትዋከብ ማምሸቷ፣ ኦሮሙማው፣ ብአዴን፣ አስረስ መዓረይ፣ ጌታ አስራደና እስክንድር ነጋ ተጠቃቅሰው እኔ ዘመዴ አስረስ ላይ የጀመርኩትን ምርመራ አቋርጬ በሌላ አጀንዳ እንድጠመድ ያመጡት ድንገቴ አጀንዳም በትናንቱ የቲክቶክ መርሀ ግብሬ አፈር ከደቼ አብልቼው ርቃናቸውን አስቀርቼዋለሁ። ኤትአባቱንስና። እግዚአብሔር ይመስገን። ተልባ ቢንጫ በአንድ ሙቀጫ አለ አጎቴ ሌኒን። ኢንዴዣ ኖ።

"…ከአሥረስ መዓረይና ከፓስተሮቹ ለዐማራ ፋኖ በጎጃም ፋኖዎች በሙሉ ምክር አለኝ። የዐማራ ፋኖ በጎጃም በአስረስ መዓረይና በጓደኞቹ አፍዝ አደንግዝ ተተብትቦ የሚያደርገው ግራ ገብቶት ፈዝዞ ተቀመጠ እንጂ ጦሩ እንዳለ ነው። ጀግንነት የአባት የእናቱ ነው። ትንሽ ጸሎት ደግሞም ጠበል፣ ዱአም አድርጋችሁ ብትንቀሳቀሱ አሸናፊነት በእጃችሁ ነው። የፋኖ መሪ የሆኑት ብአዴናውያንና ፓስተሮችን እምቢኝ በሉና ተቋማችሁን አድናችሁ ወደፊት ገስግሱ። ከጎንደር፣ ከጎጃም፣ ከሸዋና ከወሎ ወንድሞቻችሁም ጋር በፍጥነት አንድነት ፈጥራችሁ አስረስ ማዕረይና ፓስተሮቹ ብአዴኖች የዘጉባችሁን የአንድነት በር ከፍታችሁ ግቡ። ፍጠኑ።

"…እናንተም የጎንደር፣ የወሎና የሸዋ ዐማራ ፋኖዎች በአስረስ መዓረይ እና በጎጃም ፓስተር የፋኖ አመራር ብአዴኖች ምክንያት የዘገየውን አንድነታችሁን አፍጥኑትና በቅርቡ አንድ የምሥራች ለዐማራው በቶሎ አብሥሩ። አሁን ድርድሩ ውስጥ በድጋሚ ማርሸት ፀሐዩ መካተቱንም ሰምቻለሁ። ሁሉም ይስማማ አይስማማ ባላውቅም ግን አስረስ መዓረይ ወጥቶ ማርሸት ቢገባም ያው ነው። ሁለቱ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸው። እናም እንደምንም ጫና ፈጥራችሁ ፓስተሮቹን ብአዴናውያን የዐማራ ፋኖ በጎጃምን በሓሳብ አሸንፋችሁ አንድነቱን አብሥሩት ለሕዝቡ።

"…ያው ዘመነ ካሤ በድርድር፣ በውይይት ላይ ስለማያሳትፉት ብዬ ነው እንጂ ይሄ ጥያቄ መቅረብ ያለበት ለመሪው ለዘመነ ካሤ ነበር። እነ ሀብቴ ባዬ፣ እነ ምሬ አቤ፣ እነ ደሳለኝ አብደላ በወረቀት ላይ የምታወጡትን የጋራ መግለጫ መሬት ላይ ተግባር ለማምጣት ፍጠኑ። ፍጠኑ ተናግሬአለሁ። በነገራችን ላይ ቦለጢቃ በወታደር ብዛት አይደለም በፈጠነ ወሳኝ ቁርጠኛ እርምጃ እንጂ። እናንተ ባለመፍጠናችሁ ምክንያት ጋሽ ፌስታል…👆④ ✍✍✍


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
👆③ ✍✍✍ "…አስረስ መዓረይን ለማዳን ከስኳድ ጋዜጠኛ በለጠ ካሣ ጋር ቃለመጠይቅ ያደረገው ስኳድ ፋፍዴን ጌታአስራደም የከሰሰው ሻለቃ ዝናቡን እና አርበኛ ዘመነ ካሴን ለይቶ ነው። ተመልከቱ በየትም ቦታ ገብቶ መግለጫ የሚሰጠው፣ የሚደራደረው፣ የሚከራከረው፣ የሚሟገተው፣ የወታደራዊውንም አሰላለፍ፣ የምርኮ አያያዝ፣ የሒሳብ አሠራር፣ የስንቅና ትጥቅ፣ የፖሊሲ ወዘተረፈ ጉዳዮች ላይ ዘሎ የሚጣደው እኮ ዳግማዊ አቢይ አሕመድ ሴረኛውና የዐማራ ፋኖ በጎጃምን ትግልን ያቀዘቀዘው መሰሪው አስረስ መዓረይ እኮ ነው። አስረስ መዓረይ ባጠፋው ጥፋት፣ በሰራው ፋውል ቲፎዞውም፣ መንገደኛውም አፉን የሚከፍተው፣ የሚወቅሰው ግን ያን የአብርሃም በግ አርበኛ ዘመነ ካሤን ነው። በምሳሌ ላስረዳ…

"…ጋዜጠኛ ምናላቸው ስማቸውና አቶ ተፈራ የተባሉ ሁሌ ዶላር፣ ጎፈንድሚ ካለበት አይጠፌ ሰው ተጠቃቅሰው ድንገት የማርሸት አጎት ለምናላቸው የከፈተለት ነው በተባለው የግዮን ቴቪ የቴሌቭዥን ጣቢያ ላይ ቀርቦ በመሪ ጥያቄ እያጀበ አቶ ተፈሪ በጎፈንድሚ የተሰበሰበው ዶላር የት እንዳደረሰው ይጠይቀዋል። ገፋፍቶም ዶላሩ ለዘመነ ካሤ ነው የሰጠነው ብሎ ሲበጠረቅ ይታያል። በጎጃም እየተካሄደ ያለው ሴራ፣ መጠላለፍ ያልገባቸው ራሳቸው አንዳንድ ተብለው ቁጥራቸው በቀላሉ የማይገለጽ ነፍ የትየለሌ ጎጃሜዎች ደንዝዘው ይብሰከሰካሉ። ይቆዝማሉ። አብዛኛዎቹ በጎጃም ምን እየሆነ እንዳለ አያውቁም፣ አይረዱምም። በፎቶ ቦለጢቃ፣ በአክቲቪስት ጋጋታ፣ በሰበር ዜና ብዙዉን አደንዝዘውት ምኑን ከምኑ እንደሚይዘው ግራ ገብቶት ቢያንስ እኔ የማወራውን እውነት ሐሰት መሆኑን ለማረጋገጥ ወደ መሬት ወደ ቤተሰቡ ደውሎ ለማረጋገጥ እንኳ አይሞክርም። እንዴት እንዳደነዙት መድኃኔዓለም ይወቅ። ምናላቸውና አቶ ተፈሪ ዘመነ ካሤን ነው የከሰሱት። ምክንያቱም አስረስን መሪዬ እያሉት ስለሆነ ዘመነን ለማስወገድ ዘመነን መክሰስ አስፈላጊ ነው ብለው ስላመኑ ነው። እኔ ደንቃራ ሆንኩባቸው እንጂ ዘመነን ገና ድሮ ነበር የሚያስበሉት።

"…እደግመዋለሁ በጎጃም አሁን ማስወገድ የቀራቸው ዘመነ ካሴን እና ሻለቃ ዝናቡን ነው። ዘመነ አጠገብ የነበሩት በሙሉ በድሮን ተገድለው ተወግደዋል፣ ጸድተዋል። ባለፈው ዘመነንና ዝናቡን አንድ ላይ ለመግደል ፈልገው፣ ተመስገን ጥሩነህ ባህርዳር ላይ የብአዴን አመራሮችንና ካድሬዎችን ሰብስቦ "ዘመነን ገድለነዋል" ብሎ በኩራት፣ በእርግጠኝነት ሲናገር፣ የብልጽግና በቀቀኖቹ እነ ናትናኤል፣ እነ ጌትነት አልማው፣ ራሱ ፓስተር ምስጋናው አንዷለም ጭምር በቲክቶክ ውይይቱ ላይ ዘመነ አልሞተም እንጂ ተመቷል፣ ቆስሏል ይሄን አረጋግጫለሁ ብሎ እስኪቦረተፍ ድረስ ያጯጯሁትና ነገር ግን የጎንደሩ አርበኛ ባዬ ልጆች በደረሳቸው እርግጠኛ መረጃ መሠረት ለሻለቃ ዝናቡ ደውለው "ተመለስ፣ አንተና ዘመነ እንዳትገናኙ" ብለው በመንገራቸው ምክንያት ሁለቱም ለጊዜው ከመገደል ተርፈዋል። ይሄ የማወራው ውሸት አይደለም። ዘመነንም፣ ዝናቡንም የምታገኙ ሰዎች ደውላችሁ መጠየቅ እኮ ነው። ቀላሉ መንገድ እሱ ነው።

"…በነገራችን ላይ ለአቶ ምናላቸውና ለአቶ ተፈራ እስከአሁን ማንም ሰው ደፈር ብሎ የወንድ ጥያቄ አልጠየቃቸውም። ዘመነ ካሴ በላው ላሉት ገንዘብ ዘመነ የድርጅቱ ገንዘብ ተቀባይ ነበር ወይ ብሎ የጠየቀ የለም። እነ ዋን አዋራዎችም ዘመነ በግና እንጀራ ገዝቶበት በሆድ ነው የጨረሰው ያሉት ዘመነን ነጥሎ ለማስመታት ጭምር ነው። ግን እስኪ እንጠይቅ።

1. የዐማራ ሕዝባዊ ኃይል መቼ ተቋቋመ?

2. ዘመነ ካሴስ የታሰረው መቼ ነው?

3. ዘመነ ከታሰረ በኋላ ሕዝባዊ ኃይሉ በማነው ሲመራ የነበረው?

4. 20 ሺህ ያህል የዐማራ ሕዝባዊ ኃይሉ ፋኖዎች የት ገቡ?

5. ዘመነ ካሴ በጥላሁን አበጀ ጥቆማ እስር ቤት ከተወረወረ በኋላ በሴራ ከከ18 ሺህ በላይ የሚሆኑ የዐማራ ሕዝባዊ ኃይል የጎጃም ልጆች በአፋርና በጎንደር በዓከር እስር ቤት በግፍ ታስረው ገሚሶቹ የተረሸኑት እና ቀሪዎቹ አሁንም በእስር ላይ የሚንገላቱት በማን ትእዛዝ ነው?

6. አስረስና ማስረሻ ሰጤ ከተጣሉ በኋላም ሕዝባዊ ኃይሉን ያስቀጠሉት አስረስ ማረ እና ጥላሁን አበጀ አልነበሩም ወይ? እናም አስረስ መዓረይ፣ ማስረሻ ሰጤና ማርሸት ፀሐዩ ዘመዳማቾች ስለሆኑ በማርሸት አጎት በኩል ለምናላቸው ስማቸው በተከፈተ የቴሌቭዥን ጣቢያ የዘመነ ስም በድፍረት እንዲጠፋ ለምን ተፈለገ?

7. ዘመነ ካሴ ከእስር ቤት ከተፈታ በኋላ ከማናቸውም የበፊት ሴረኛ ጓዶች ጋር ሳይገናኝ ባህርዳር እረፍት ላይ እያለ ቤቱን አስከብበው በሞርታር ሲያስመቱት በፈጣሪ ቸርነት አምልጦ ብቻውን ተሰውሮ ገለል ብሎ ተቀምጦ አልነበረም ወይ?

8. አስረስ መዓረይስ ከዚያ ሁሉ ሴራው በኋላ ዘመነን እንዴት? ለምን? አፈላልጎ አግኝቶት ለምኖት ታረቀው?

"…በወቅቱ እኮ አዝማሪት አልማዝ ባለጭራዋ የምትመራው የምሥራቅ ጎጃም የሳይበር የብአዴን ቡድን አርበኛ ዘመነ ካሤን በማንቋሸሽ፣ በማዋረድ እና በመሳደብ፣ አልማዝ ባለጭራዋ እንዲያውም የዘመነን ፎቶ ቀሚስ አልብሳ፣ ሰድባ ለሰዳቢና አጋሯ ለሆነው ለጎንደሩ ስኳድ አሳልፋ ስትሰጠው አልነበረም ወይ?የስድቡ ዓላማና ተልዕኮ እኮ አርበኛ ዘመነ ካሴ ከእስክንድር ነጋ፣ ከኮሎኔል ፋንታሁን ሙሃቤና አርበኛ ሰፈር መለስ ጋር በጋራ ለመሥራት የመሰረቱት የፋኖ ሠራዊት ይፋ መሆኑን ተከትሎ እኮ ነው። ለዚያ ነው በቀጥታ ከአስረስ ማረ በወረደ ትእዛዝ ዘመነ ካሴ በኦሮምቲቲዋ ሸንጎ በአዝማሪት አልማዝ ባለጭራዋ ሲዋረድ፣ ሲሰደብ የነበረው።

"…ወዲያው አይደለም ወይ አስረስ መዓረይ ትግሉ ምንም ዓይነት ደረጃ ላይ ባልደረሰበትና ዐማራው ሁሉ ባልወሰነበት ሰዓት ራሱን የፋኖ አመራር አድርጎ በመሾም፣ እንደራደራለን የሚል ቃለ ምልልስም ቢቢሲ ላይ መስጠቱን ተከትሎ ዐማራው ዳር እስከዳር ተነሥቶ "ጥንብ ብአዴን፣ የምን አባህ ድርድር ነው?" ብሎ ሲያወግዘው የሚዲያ ትችትን እንደ ጦር የሚፈራውና መቋቋም የሚያቃተው በቀቀኑ አስረስ መዓረይ ሲከንፍ ገስግሶ ዘመነ ካሴ እግር ላይ ወድቆ ይቅርታም ጠይቆት፣ "ዘሜ አንተው ምራን" በሚል ከዘመነ ጋር እርቅ ፈጥሮ ከዐማራ ሕዝብ የተነሳበትን ተቃውሞ ማዕበል ዘመነን ካባ ስር ተወሽቆ በማምለጥ ዛሬ ዘመነን ከፊት ገትሮ በእሳት እያስለበለበ የሚገኘው። የፎቶ መዓት እያነሣው በእነ እስማኤል ዳውድ ኢንድሪስ ሁላ ሲያሰድበው የሚውለው።

"…የምንላቸው ስማቸውና የአቶ ተፈራ የተሰበሰበው ገንዘብ የት ደረሰ? የሚል ቃለምልልስ እዚህ ጋር ነው የሚነሳው። በቅድሚያ ቃለምልልሱ አሁን በዚህ ጊዜ ለምን ተነሣ? በመቀጠል የዐማራ ሕዝባዊ ኃይልን ዘመነ ከታሰረ በኋላ ሲያስተዳድሩት የነበሩት አስረስና ጥላሁን ሆነው ሳለ ከ4 ዓመታት በኋላ ዘመነ ካሴና ማስረሻ ሰጤን ሁለቱን ብቻ በተለየ ሁኔታና በሌሉበት ምናላቸው ለምን ስማቸውን ማንሣት ፈለገ? ሌላው እነ ምኔና ጋሽ ተፌ የተጣረሰባቸው፣ ሳይማከሩም አየር ላይ ያዋሉትና የተፎገሩበት ደግሞ በወቅቱ የዐማራ ሕዝባዊ ኃይል የነበረው ጎጃም ውስጥ ብቻ ሆኖ ሳለ የተዋጣውን ገንዘብ ለሌሎች በዐማራ ግዛቶች ውስጥ ለሚገኙ ፋኖዎች ዘመነ ስላላካፈላቸው እጃችን ላይ የቀረውን ገንዘብ ለሸዋ ሁለት አደረጃጀት ለወሎ ሁለት አደረጃጀት ሰጥተን ጎንደር ላይ ለባዬ ቀናው የቀረችንን 5ሺህ ዶላር ልንሰጠው እያጠናን ነው ብለው የደሰኮረቡት መንገድ ነው። እዚህ ላይ ነው የተፎገሩት አርቲስቶቹ ተፌና ምኔ። 😂 ለመሆኑ የዐማራ ሕዝባዊ ኃይል ማስረሻ ሰጤና ዘመነ ካሴ አስረስ ማረ ጥላሁን አበጀ በሚመሩበት ወቅት… 👇③✍✍✍


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
👆② ✍✍✍ "…ብልፅግናው የኦሮሙማ ገዳይ ሴረኛ በኤልያስ መሠረት በኩል ይሁነኝ ብሎ የጎጃም ስም እንዲካተት በማድረግ ጎጃሞች የተጠቅተናል፣ ድሮም የተዘመተብን ለዚህ ነው፣ ዘመድኩን ጎጃም ገብቶ አስረስ መዓረይን የየነከሰብን ለዚህ ነው። እናም መሪያችንን እንታደግ ብለው የሸንጎ ሠራዊት መዓት እሪሪ እንዲል አስደረጉት። የዐማራ ፋኖዎች በአጠቃላይ በአንድ ድምጽ የእስክንድርን አካሄድ በመግለጫ ቢያወግዙም አስረስ መዓረይ ግን በዚያ ስለተሸፈነ፣ ራሱን ለማዳን ሲል ራሱ በድምፅ ተቀርጾ ድርድር ተብዬውን አምርሮ እንደተቃወመ አድርጎ አሰራጨ። ሲጀመር ድርድር መኖር ያስፈልጋል ብሎ ከእስክንድር በፊት ከአንድ ዓመት ተኩል አስቀድሞ ለቢቢሲ አማርኛው ክፍል ቃሉን ሰጥቶ በራሱ ላይ ማእበል፣ ሱናሚ ፈጥሮ፣ ደንግጦ ዘመነ ካሤ ካለበት ስፍራ ድረስ ሄዶ እግሩ ላይ ወድቆ ምራን ብሎት ወደፊት አምጥቶት "ዘመነ ድርድር የሚባል የለም" ብሎ እንዲናገር አድርጎ መትረፉን ረስቶ አሁን እስክንድርና ቡድኑን ከሳሽ ሆኖ ብቅ ይላል። አስረስ ከስኳድ ጋር እየመከረ ከእስክንድር ርቄአለሁ ቢል ሐሰት ነው። ከሥጋው ጦመኛ ነኝ ከመረቁ ስጡኝ እንደማለት ነው።

"…ኧረ በስመ ሥላሴ። ተራወጡ እኮ። ድርድር፣ ውይይት፣ ምክክር፣ ጲሪሪም ጳራራም፣ ብለው የሌለ ወከባ ሲፈጥሩ ሳይ እኔ ዘመዴ በሳቅ ፍርፍር ነው የሚያምረኝ። አሜሪካ ገብቷል፣ አንዴ እንግሊዝ ኤምባሲ ታይቷል፣ ብላ ብላ ብለው በባዶ ሜዳ የሚክቡት እስኬውን፣ የፖለቲካ ሞት ከሞተበት፣ ከተቀበረበም መቃብር አፅሙን አውጥተው የሌላ የመጬ ጀግና ጀግና ለማጫዋት ሲሞከሩም ሳይም ኧረ ላሽ። ኢደብራል።

"…እስክንድር ራሱ ቢጨንቀው በአቢይ አሕመድ መካዱ ሲያስደነግጠው፣ እነ ሀብታሙ አያሌው፣ እነ አበበ በላው ተመልካች እንደሌላቸው፣ የእነ ፓስተር ምስጋናው ጣና ቴቪም እንደማያዛልቀው አውቆ በቀጥታ ቲክቶክ ገብቶ ከጃል ሀብታሙ በሻህ ጋር ታብ ታብ ሲያስደርግ ነው ያመሸው። እስክንድር ከዝርክርኩ ሀብታሙ በሻህ ጋር ሲነጋገር ዘመዴ በቲክቶክ 4:45 ኛው ሰከንድ ላይ ጃል ሀብታሙ ለእስክንድር የደወለበት የስልክ ቁጥር ሁሉ ይታያል። እስከዚህ ድረስ ነው የተዝረከረኩት። ቀሽሞች። አትድኑም አልኳችሁ። በዐማራ ሕዝብ ወጣቶች ደም ቀልዳችኋልና አትድኑም። የንፁሐን ደም እረፍት፣ እንቅልፍም ያሳጣችኋል። ተቅበዝባዥ፣ ባካኝ፣ ባተሌ ነው የምትሆኑት። እንደ ተራወጣችሁ ነው የምትኖሩት፣ የምትቀሩት።

"…ይኸውላችሁ ሁልግዜ እንደምለው የብአዴን ዋና ልቡ ያለው ምሥራቅ ጎጃም፣ ደቡብ ጎንደር እና ደቡብ ወሎ ነው። ወያኔ በትግራይ ሞታ ብትቀበር እንኳ አይተ በረከት ስምኦን በምሥራቅ ጎጃም፣ በደቡብ ጎንደርና በደቡብ ወሎ ጠፍጥፎ የሠራው ሃይ ኮፒ አማርኛ ተናጋሪው ዐማራ መሳይ ሆዳም፣ አጋሰስ አሞራ ብአዴን የአባቴ በአካል ወያኔን ተክቶ የሚኖረው በእነዚህ አካባቢ ነው። ወያኔ ከትግራይ የስም አጠራሯ ቢደመሰስ እንኳ ወያኔ የወያኔ ልጅ ነኝ ብሎ ወያኔን ተክቶ ነፍስ ዘርቶ በመነሣት ዊኒጥ ዊኒጥ ለማለት መሞከሩ አይቀርም። የዐማራው አዚሙ፣ ትብታቡ፣ አስማቱ ስለተገፈፈለት፣ የሱዳንም፣ የናይጄሪያና የዓረብም ጥንቆላና ሟርቱም ስለከሸፈለት አበደን የድሮውን ቢጭኑት አህያ፣ አጋሰስ፣ ቢጠምዱት በሬ የሆነ ዐማራን ዳግም ማግኘት አይቻልም። አበደን አልኩህ።

"…ብአዴን በመሰሪው አስረስ መዓረይ በኩል የዐማራን አንድነት የመበተን፣ የማዳከም ተግባር ነበር ተልእኮ ሰጥተው በዚያ በኩል ነበር ተስፋ አድርገው የተቀመጡት። ስንቱን ጀግና የጎጃም ዐማራ አስቀጥፈው አስበልተው፣ አድቅቀው፣ ሕዝቡን ከወያኔ እኩል ወደ ኋላ እንዲቀር ከትምህርት አስቀርተው፣ አደንቁረው ማይምም አድርገው፣ መምህራኑን ተፈራርቀው ገድለው ጨፍጭፈው፣ ነጋዴው ሀገር ለቆ ብርርር ብሎ እንዲወጣ አስደርገው፣ ባዶ መሬት ኦሮሙማው ወርሶ እንዲቀመጥ አመቻምቸው ሁሉን ጨረስን ብለው ሲያበቁ ባልጠበቁት መንገድ፣ ባልጠበቁት ሰዓት በእኔ በዘመዴ በኩል የላኩት መሰሪ ድብቅ የሳር ውስጥ ኮብራ እባብ ተደብድቦ፣ ተወቅጦ፣ ተቀጥቅጦ መርዙን ተፍቶ ከሽፏል። ይሄን የሞተ አካል ነው እንግዲህ ብልፅግና ሸንጎና ስኳድ ተናብበው እስክንድርንና አስረስን የሲሻል ሚዲያ ራምቦ፣ ሸዋዚንገር አድርገው ለማሯሯጥ የፈለጉት።

"…አበደን እኔ በበኩሌ ዓይኔን ከጎጃም አላነሣም። የሞተ፣ ሞቶም የተቀበረው የእስክንድር ጉዳይ ምን ኃይል አለውና ነው የማጯጩኸው። አቢይ አሕመድም ሆነ ራሱ እስክንድር ነገም ይሁን በአፍቃሬ ወያኔው ጢም አልባው ኤልያስ መሠረት ሚዲያ በኩል የነዙት ፕሮፓጋንዳም በቀጥታ አስረስ መዓረይንም ለማዳን ነው ባይ ነኝ። የብአዴንን መጋጋጥ ነው ያየሁበት። ምን ማለት ነው? እስክንድር ለኤሊያስ መሰረት ሚዲያ ተናገረ በተባለው ቃል ላይ "…በመንግሥት በኩል ደግሞ ትጥቅ በመፍታት ወደ ማሰልጠኛ መግባት፣ ጎጃም አካባቢ ላይ ያለውን ነገር ማስተካከል፣ በየከተማው ያለውን አደረጃጀት መረጃ መቀበል፣ ተጠያቂ የሚሆኑ አባላቱን አሳልፎ መስጠት እንዲሁም በምክክር ኮሚሽኑ ውስጥ መካተት ናቸው ተብሏል ማለት? KKKKK "…ጎጃም አካባቢ ላይ ያለውን ነገር ማስተካከል" አላለም። ምኑን ነው የሚያስተካክለው? በፈረንሳይኛ ይሄ ማለት "ዘመዴም ጎጃም ገብቼ አልወጣም ያለው፣ እስክንድርም ጎጃም ይስተካከል የሚለው ሁለቱም ብልፅግና ልኳቸው የጎጃምን ፋኖ ለማፍረስ ነው የሚል የተጠና ነገር ግን ቀሽም ፕሮፓጋንዳ በመልቀቅ ጠምጄ የያዝኩት የአስረስ መዓረይን ኔትወርክ አፈር ከደቼ እንዳላስግጠው አባውን ለመታደግ በራሱ በብልፅግና በኩል የተዘጋጀች ያረፈደ የበሻሻ አራዳ አጀንዳ መሆኑ ነው። ሊበላ…?

"…እስክንድር እዚያው ሸዋ ይሁን ደቡብ ወሎ፣ አልያም እንግሊዝ ኤምባሲ ይሁን አሜሪካ ኤምባሲ፣ ወይም ደግሞ አሜሪካ ከመግባቱም በፊት እሱ የነበረው 4 ጠባቂ ብቻ ነበር። ከጠባቂዎቹ መካከል አንደኛው የጎጃም ተወላጅ የሆነው የግል ጠባቂው ባለፈው ወር ነው ከሸዋ ተነሥቶ ወደ ጎጃም የተመለሰው። እና እስክንድር በምን ጦሩ ነው ከጎጃም ጋር የሚዋጋው? ጎጃምንም የሚያስተካክለው? ጭራሽ ከጎጃም ተዋርዶ፣ አንዳንዶች ባልተረጋገጠ መንገድ እንደሚሉት ለእነ አስረስ መዓረይ ቡድን 12 ሚልዮን ብር ከፍሎ ከጎጃም ለቅቆ ሸዋ ፈርጥጦ መደበቁን፣ በዚህም ምክንያት እኮ ነው የእስክንድር ደጋፊዎች በሙሉ ከስኳድ ጋር አብረው ጎጃምን እነወደ ሕዝብ፣ የዐማራ ፋኖ በጎጃምን እንደተቋም፣ ዘመነ ካሤን እንደ መሪ ሲያበሻቅጡ፣ ጎጠኛ፣ ዘረኛ፣ ብአዴን፣ ወያኔ እያሉ ዋይዋይ ሲሉ የሚውሉት። ሙሃቤ እንደሁ አጃቢ ሲቀርለት ጦሩ ከምሬ ተቀላቅሏል። ማስረሻ ሰጤ ነፍሴ አውጪኝ ብሎ ደቡብ ወሎ ተወሽቆ መኪና ቀረጥ እየቀረጠ እንዲተዳደር የተፈቀደለት ሰው ነው። በምኑ ነው ጎጃምን የሚያስተካክለው። የሚያስቆመውም። ጎጃም እኮ በእነ አበጀ በለው፣ በእነ ጥላሁን አበጀ፣ በእነ ፓስተር ዳዊት፣ በእነ ፓስተር ተፈሪ ካሳሁን፣ በእነ አስረስ መዓረይ የሴራ ጠፈር ቀፍድደው አስረው ሽባ ዲሞራልይዝ አድርገውት አላላውስ ብለውት እንጂ የጎጃም የአንድ ጎጥ የአንድ ቀበሌ ፋኖ እኮ ብቻውን ዓባይን ተሻግሮ ሰላሌ ሜዳ ላይ ከብልጽግና ሠራዊት ጋር ብቻውን መፋለም ይችል ነበር። ይቺን ይቺን ነገር ለአማትህ ንገር ኤሊያስ መሠረትም እስክንድር ነጋም፣ አስረስ መአረይም ድንጋይ ብሉ። 👇② ✍✍✍


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
"ልዩ ርእሰ አንቀጽ"

"…በዚህ ሁሉ ሩጫ፣ በዚህ ሁሉ ግርግር መሃል እውነቱ፣ ሃቁ ፍንትው ብሎ እንደ ንጋት ጮራ ፍንጥቅ ብሎ እየወጣ ነው። የመጨረሻው የዋንጫ ጨዋታ ስለሆነ ፍትጊያው፣ ሴራው፣ ጥሎማለፉ፣ ፋውሉ ይበዛል። ደግሞም ጨዋታው ዋንጫውን ለማግኘት ስለሆነ ሁሉም አለኝ የሚለውን ችሎታውን ከውስጡ አውጥቶ ይጠቀማል። ያሳየናልም። እስከዛሬ ሁሉም የፋኖ ተወካይ ነን ብለው ወደ አማሪካ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ተሳፍረው ሄደው በዚያው በአማሪካ የሎቢ ሥራ ከዲሞክራቶቹ ጋር ይሠሩ፣ እንዘጭ እንዘጭ ሲሉ የከረሙት፣ ስቴት ዲፓርትመንት ደጅ እየጠኑ የከረሙት በሙሉ፣ በእነ ብሊንከን ሲጋበዙ፣ ሲሰለጥኑ የነበሩት በሙሉ አሁን በትራምፕ አስተዳደር ስለማይፈለጉ በጊዜ ጥጋቸውን ይይዛሉ አልያም እኔ ከሞትክ ሰርዶ አይብቀል በማለት የዐማራ ፋኖን ትግል ለማኮላሸት ከገማው፣ ከከረፋው፣ ከበሰበሰው ብልፅግና ጎን በጥበብ ተሰልፈው ትግሉን ለመጎተት በትበት ይላሉ። እነ እስክንድር፣ እነ ዋን አዋራዎች፣ ጋሽ ልደቱ፣ የወያኔ ሰዎች በጠቅላላ ከዲሞክራት ጋር የሎቢ ሥራ ሲሠሩ የከረሙት በሙሉ አሁን ዋጋ ምንም ዋጋ እንደሌላቸው ተረድተው በአንድ ቅርጫትም ከዚህ በኋላ ምንም ዋጋ እንደሌላቸው ስለተረዱት ነው ድርድሩን የሚያሯሩጡት።

"…ማወቅ የፈለግኩት የእነ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ሓሳብ ነበር። አንዳርጋቸው ፅጌ መሳይ መኮንን ላይ ቀርቦ እስክንድርን በስም ባይጠቅስም የድርድር አካሄዱን አውግዟል። መሳይም ከሌላው ጊዜ በተለየ መልኩ የጋዜጠኝነት ጥጉን አሳይቶበታል። ሁለቱም በድምዳሜያቸው እስክንድር የዐማራን ሕዝብ ሸውዶ ድርድር ብሎ ነገር የለም። የዐማራን ሰቆቃ አሳወቅን ብሎ በጀርባ ግን መሰረት ሚዲያ እንዳጋለጠው አሜሪካ ወይ አውሮጳ እንደራደር ማለቱ ትልቅ ክህደትና ወንጀል ነው ሲሉ ተደምጠዋል። ይሄን ያዙልኝ። እንቀጥል።

"…አጅሬ እስክንድር የሰሜን ሸዋና የደቡብ ወሎ ጫካ ሰልችቶት፣ የዳያስጶራውም ዶላር ጠሮበት፣ የሚያዋጋውም ጦር ተኖበት እና የጎጃም ፍሬንዱም እስስት መርዛም እባቡ አስረስ መዓረይም በእኔ በዘመዴ ስለተጋለጠበና ፍፁም በማይድን የቦለጢቃ ህመም ታምሞ ፍፁም የሆነ የፖለቲካ ሞት መሞቱን በማረጋገጡ በድርድር ስም አማሪካውያንም ሆኑ አውሮጳውያን ነፍሱን ታድገው፣ ከጫካም አውጥተው በቦሌም ሆነ በባሌ አሜሪካ አልያም አውሮጳ እንዲወስዱትና ሕይወቱ እንዲተርፍ ወስኖ ያደረገው ይሆናል ብለን ብንገምት ስህተት አይሆንብንም።

"…ሌላው አሳዛኝ እውነታ ግን አብይ ያሰላው ስሌት ነው። እስክንድር ወደ ድርድር ለመምጣት ቢወስንም የዐማራ ሕዝብ ክህደቱን ካወቀበት፣ ሌሎች ሃቀኛ የፋኖ መሪዎች ለመደራደር መወሰኑን ካወቁበት ከፍተኛ ችግር ውስጥ እንደሚገባ እና ለዚህ መፍትሄ ጠይቆ ጉዳዩ በምስጢር እንደሚያዝና እስክንድርም፣ ቃል አቀባዩም ወደ ሚዲያ ወጥተው ዐማራን እንዲሸውዱና ጉዳዩ በዛ ይቀዛቀዛል ብሎ በመከረው መሰረት ያን ማድረጉ ነው። ነገር ግን ከሃዲ ይሁዳው አብይ አሕመድ ምስጢሩን በጓሮ በር ለወያላው መሰረት ሚዲያ ምስጢሩን አሾልኮ እንዲደርስ በማድረግ ሌሎች የዐማራ ፋኖዎች በወፈፌው እስክንድር ላይ መግለጫና ውግዘት እንዲያወርዱበት አስደርጎ፣ ያሰበው ሴራ በመሳካቱ በቀጣይ እስክንድርን ነጋን አሳዶ በመግደል ይኸው ሊደራደር ፍላጎት ያሳየውን የፋኖ መሪ አሸባሪዎቹ ፋኖዎች ገደሉት ብሎ ለማርኮ ሩቢዮ እስክንድርን በአካል ለሚያውቀው ለማቅረብ ያቀዳት እጅግ አደገኛ ዕቅድ ነች።

"…እስክንድር እንደሚወራው እንግሊዝ ወይም አሜሪካ ኤምባሲ ተጠልሎ ካልተደበቀ፣ ወይም አውሮጳ ወይ አማሪካ ገብቶ ካልሆነ በቀር፣ አብይ አሕመድ አሁን እስክንድር ነጋን ወይ ደብዛውን ያጠፋዋል አልያም ያለ ጥርጥር ይገድለዋል። እነ አምባቸውን፣ እነ አሳምነው ጽጌን፣ እነ ሰዓረ መኮንን እንደገደላቸው ይገድለውና ቦለጢቃ ይሠራበታል። ከዚያስ ከዚያማ ማርኮ ሩቢዮ ሆይ… ያ አንተ ምታውቀው የነፃነት ታጋይ እስክንድር ነጋ የተባለ ጀግና አርበኛ ከመንግሥት ጋር እደራደራለሁ፣ እነጋገራለሁ ስላለ በሌሎች ድርድርን በማይሹ ጽንፈኛ አሸባሪዎች ተገደለ። ማስረጃም ለፈለግክ ይኸው ያወጡበትን መግለጫ ተመልከት በማለት ለአዲሱ ለትራንፕ አስተዳደር እስክንደር ነጋን መስዋእት አድርጎ ሽብርተኝነትን በጋራ እንከላከል በማለት ሊጎዘጎዝ ይችላል። ለዚህም እስክንድር በዐማራ ፋኖም ሆነ በዐማራ ሕዝብ የበለጠ እንዲቀጠቀጥ ብልፅግና በራሱ አክቲቪስቶች በኩል እስክንድርን ወዳጅ አድርጎ በማቅረብ እንዲጽፉበት እያደረገ ነው። እኔም የዐማራ ኃይሎች እስክንድር ላይ ከዚህ በላይ ትኩረት ሰጥተው ባይንቀሳቀሱ፣ ስለእሱም ባያወሩ ሁላ ብዬ እመክራለሁ። እዚያው እንደ ፍጥርጥሩ ይሁን። እነርሱ ሥራቸው ላይ፣ አንድነታቸው ላይ ቢያተኩሩ የተሻለ ነው ባይ ነኝ።

"…በዚህ አጀንዳ የተሸበሩት የጎጃሙ አስረስ መዓረይ ያሰማራቸው የሳይበር ቅጥረኞች እና እስክንድር ነጋ ራሱ ነው የተጨነቁት። የአቢይ አሕመድ የሳይበር ሠራዊት ሳያስቡት ማኖ አስነክቶ አተራመሳቸው ነው። ብሩክ ይባስ እስክንድርን ቃለ መጠይቅ ሲያደርግለት "ድርድሩ እንዴት ነበር? ብሎ ድርድር እንደተደረገ አድርጎ ሲጠይቀው እንመለከታለን። እስክንድር ግን ድርድር የሚለውን ቃል አልወደደውም። እናም ብሩኬን "ድርድር እኮ አይደለም ውይይት ነው" ብሎ ለመሸወድ ሞከረ። የሆነው ሆኖ በራሱ በእስክንድር ግሩፖች ሳይቀር ቅራኔ ንትርክ ነው የተፈጠረው። እንደ ፍጥርጥራቸው። ሥራቸው ያውጣቸው። የአስረስ መዓረይ ክሊኮችም ይህቺን አጋጣሚ ተጠቅመው መሰሪውን አስረስ መዓረይን ለመታደግ ሲራወጡበት ታይተዋል። ዓስረስ መዓረይ ጫካ ውስጥ ቢጮህ፣ ቢፈራገጥ የሚሰማው ቢያጣ ጮቄ ከተራራው ላይ ወጥቶ እዬዬ፣ ኡኡ፣ እሪ ድረሱልኝ ብሎ ነው የተጣራው። እነ አልሚ ባለጭራዋ፣ እነ ተስፍሽ ወዲ ወልደ ሥላሴ፣ ይሄነው የሸበሉ፣ ጠቋር አማኑኤል አብነት፣ ሰጣርጌ፣ ሁሉም ተንጫጩ፣ እሪሪ ኡኡ አሉለት። እንዲያውም ወዲ ወልደ ሥላሴ ለመዓረይ ግጥም ሁላ ገጠመለት።

ጮቄ ተራራው ላይ ሥሩለት ሰገነት
ከአናቱ ላይ ቁሞ ሸገርን ይይበት !
ጠበቃው 💪

… በማለት ነው የገጠመለት። ከምሥራቅ ጎጃም፣ ከደብረ ማርቆስ ፈርጥጦ፣ ቀበሌውን ለብራኑ ጁላ ሽንኩርት አራዊት ሠራዊት እና ለገጠር ሚሊሻ ለቅቆ ጮቄ ተራራ ላይ ኤኮ ቱሪዝም አስተዋዋቂ ባለሙያ ይመስል ተጎልቶ ከዚያ ከጮቄ ተራራ ላይ ሁኖ አዱ ገነት ይያት እንጂ ዓባይን ተሻግሮ ወደ አዲስ አበባ  መግባት አትችልም ሲያምርህ ይቅር ብሎ በደብረ ዓባይ ቅዳሴ ዜማ የገጠመለትን ግጥም ለጥፎ ለመዓረይ ልጅ ለአስረስ ገጥሞለታል። እንጦጦ ላይ ሲጠበቅ ጮቄ ላይ ይደብራል። በበግ የሚመራ የአንበሳ መንጋ ትርፉ ጮቄ ተራራ ላይ ተጎልቶ፣ ተወዝፎ፣ ተዘፍዝፎ መሳቂያ፣ መሳለቂያ መሆን ነው። በፉከራ፣ በግጥም፣ በፎቶ ቦለጢቃ የሚሆን ነገር የለም። የሕልም እንጀራ አያጠግብም። ላም አለኝ በሰማይ ወተቷንም አላይ አይሁን የጎጃም ፋኖ ጉዞ። አቅም፣ ወንድነት፣ ጀግንነት ሳይጠፋ በበግ በተኩላ እንዴት ተቋሙ ይመራል? አስተካክሉና ሩጫውን ጀምሩ። እየመከርኳችሁ ነው። አስረስ መዓረይ ሲነግስ እኛ እሱን ተጠግተን ያልፍልናል የሚሉ ደናቁርቶችን እየተከተላችሁ አትደንዝዙ። ንቃ ጎጃም። የበላይ ዘር ንቃ።…👇① ✍✍✍


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
መልካም…

"…ነገ ከራየን ወንዝ ማዶ ወጣ ብዬ ስለምውል ዛሬ በእረፍቴ ቀን ይሄን ድርድርና ግርግር በተመለከተ ልዩ ርእሰ አንቀጽ ብለቅባችሁ ምን ይላችኋል…? 😂


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
"…አንቺ ከዳተኛ ልጅ ሆይ፥ እስከ መቼ ትቅበዘበዣለሽ? ኤር 31፥22 "…ብርሃንም ሳይኖር በጨለማ ይርመሰመሳሉ፤ እንደ ሰካራም ይቅበዘበዛሉ። ኢዮ 12፥25

• እንደምን አደራችሁ?
• እንደምን አረፈዳችሁ?
• እንደምን ዋላችሁ?
• እንደምን አመሻችሁ?

• መልሱ እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
"…አዳሜና ሔዋኔን ለማስነጠስ ወደ ቲክ ቶክ መንደራችን ልመጣ ነኝ…😂


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
እስቲ ተወያዩበት…✍✍✍

"…የሆነ ጊዜ እስክንድር ነጋ በወለጋ ዐማሮች ላይ ፍላጎት አሳይቶ ቦለጢቃ ሊሠራባቸው ሞክሮ ከሸፈበት። ቀጠለና ሙላት አድኅኖ ከኡጋንዳ የተሳሳተ መረጃ አውጥቶ ተቃውሞ ሲበረታበት የወለጋን ዐማራ ይቅርታ ጠይቆ ጮጋ አለ። ፩ በሉ።

"…ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ድሮን አይጎበኜው፣ ጥይት አይነኬው፣ አክተር አይሞትም ሸዋዚንገሩ፣ 24/7 ኢንተርኔት ተጠቃሚው፣ የግንቦት ሰባት ዋነኛው ሴል፣ ፀረ ዐማራ ፋኖው፣ አርበኛ ዘመነ ካሤ ባሕርዳር ጠቁሞ ያሳሰረው፣ አጠገቡ ያሉት የዐማራ ፋኖ በጎጃም ጀግኖችን በሙሉ አስቀርጥፎ የሚያስፀዳው ጥላሁን አበጀ ወለጋ ድረስ በደመና፣ በአየር ተጭኖ ገብቶ የወለጋ ፋኖ ዕዝን መሥርቻለሁ ብሎ ከች አለ።

"…ጥላሁን አበጀ ምሥራቅ ጎጃም ሸበል በረንታን ለብአዴን ሚሊሻ አስረክቦ ወደ ምዕራብ ጎጃም ፈርጥጦ የተደበቀ፣ የበላይ ዘለቀን ሃውልት ቀሚስ ያስለበሰ፣ ጀግና ጎጃሜዎችን ቀርጥፎ ያስበላ፣ ከአስረስ መዓረይ ጋር በመሆን ትግሉን ፌስቡክ ላይ ያስቀረ ሾተላይ ሰው ነው።

"…የእኔ ጥያቄ የወለጋ ፋኖ በጎጃም ፋኖ ስም በእነ ጥላሁን አበጀ በኩል የተቋቋመው ለወለጋ ዐማራ ምን ደግሰውለት ነው? ጥላሁንስ እንደ እስክንድር በግማሽ ቀን ከጎጃም ወለጋ የሚመላለሰው በመንፈስ ነው ወይ?

"…ትናንት በማርሸት ፊርማ የወጣ ደብዳቤ አለ። ተራም ይሁን ከፍተኛ አመራር ከድርጅቱ ዕውቅና ውጪ አንድም ሰው ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ምንም እንዳይለጥፍ የሚል መመሪያ መውረዱን ሰምተናል። መመሪያው ዝናቡ የፋኖ ዮሐንስን መገደል ምክንያት አድርጎ እሱን ተከትሎ የመጣ ነው ቢሉም ነገር ግን ይኸው ጥላሁን አበጀና አበጀ በለው ገሬ ሁለቱም እንደ ልባቸው ነው የሚንፏለሉት?

• ሰፈሩን ነፃ ሳያወጣ ዓባይና ግቤን ተሻግሮ ወለጋ፣ ወለጋ ማለቱን እንዴት አያችሁት? …የሚሳደብ ያው ምሱን ይቀምሳል። 😂


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
ጎጄ መሪዎችህን ጠብቅ።

"…ስኳድ በለጠ ካሣ ዛሬ ከስኳድ ፋፍዴኑ ጌታአስራደ ጋር ያደረገው መርዘኛና በሴራ የተሞላ ቃለመጠይቅ ነው። ዝርዝሩን ማታ በቲክቶክ መርሀ ግብሬ እመጣበታለሁ።

"…ተመልከቱ በለጠ ካሣ በርእስ መልክ ያስቀመጠው የዐማራ ፋኖ በጎጃም ወታደራዊ አዛዡን ሻለቃ ዝናቡንና የዐማራ ፋኖ በጎጃም ዋና ሰብሳቢ አርበኛ ዘመነ ካሤ ን ነው ለማስጠቆር የፈለገው። የስኳድን መናበብ እዩልኝ። ተመልከቱልኝማ።

"…የአስረስ መዓረይ የልጆቹ እናት ሚስቱ ደቡብ ጎንደሬ ናት። ያውም የአንድ ፋኖ አደረጃጃት መሪ እህትን ናት ተብሏል። አስረስ መዓረይ የሦስቱን የዐማራ ግዛት የዐማራ ፋኖ አንድነት ያዘገየ ሾተላይ ነው። አሁን ግን ስኳዱ አስረስን ከደሙ ንፁሕ አድርጎ ዘመነንና ዝናቡን በመክሰስ ብቅ አሉ።

"…ሻለቃ ዝናቡን እነ ናትናኤል መኮንንም በደምበጫው የብአዴኖች ርምጃ እየከሰሱት ነው። አቶ ምናላቸው ስማቸውና አቶ ተፈራም እነ አስረስ መዓረይ፣ እነ ማስረሻ ሰጤ ቀርጥፈው የበሉትን ብር በዘመነ ካሤ እንዲያላክኩ ነው የተደረገው። እነ አልማዝ ባለጭራው በተለየ ሁኔታ ዘመነን እንዲሰድቡ የሚደረጉትም በምክንያት ነው። አሁን ጭራሽ ፋፍዴን አስኳድ ዘመነንና ዝናቡን ለማስጠቆር ጓ ብለው መጡ።

"…ለእኔ ሴራው ይገባኛል። ይሄን ሴራ በቴሌቭዥን ነበር ፍርስርሱን ማውጣት የሚቻለው። ነገር ግን አስረስ መዓረይ ከመረጃ ቲቪው አስረስ ግርማ ካሣ ጋር ተመሳጥሮ የሕዝብን ሴራ የማክሸፍ መብት እንዲሞት ፈረዱብት። ቢሆንም ግን እኔ ዘመዴ ይሄንንም በቴሌግራምና በቲክቶክ ቻናሌ ከፈጣሪ ጋር እናፈርሰዋለን።

"…አስረስ መዓረይ ለእኔም ያለኝ ይሄንኑ ነው። ለአንድነቱ ከእኛ በኩል እንቅፋት የሆነብን ዝናቡ ነው ነበር ያለኝ። ዝናቡ ደግሞ ይሄ ነገር አልገባኝም በድርድሩ ላይ ዘመነ ለምን አይገኝም ሲል ታስታውሳላችሁ።

•አይገርምላቹም?


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
ማስታወቂያ…

• ጌዴዎናዊነት አሸናፊነት ነው።

"…ዛሬ ምሽት በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ "ነጭ ነጯን ከዘመዴ ጋር" የተሰኘው ዝነኛ መርሀ ግብራችን በቴሌቭዥን እስክንከሰት በቲክቶክ ይዤላችሁ እቀርባለሁ።

• ከእውነት ጋር በቁርባን በቃልኪዳን ተጋቡ። ከእውነት ጋር ከተጋቡ በኋላ መፋታት ነውር ነው። ኃጢአትም ነው።

"…ሥራ ልሥራ ካላችሁ አንዲት የስልክ ስታንድ፣ አንዲት ቀላል ስልክ እና የኢንተርኔት ኔትውርክ ካለ በቂ ነው። ከአጠገብህ ምስለ ፍቁር ወልዳ፣ መጽሐፍ ቅዱስ፣ ድርሳነ ሚካኤል፣ በኩባያ ውኃ፣ የማስታወሻ ደብተር ትይዛለህ ከዚያ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አንደበትህ ላይ ሆኖ እንዲናገር መፍቀድ፣ ኃይሉን፣ ጽናቱን፣ ብርታቱንም፣ ዕወቀትንም ይገልጽልህ ዘንድ መማጸን ነው። ከዚያ ከዚያማ እርሱ ሥራውን ሲሠራብህ ማየት ነው።

• እውነት እግዚአብሔር ነው። እግዚአብሔር ደግሞ አሸናፊ ነው።

"…የ EBC, FANA, WALTA, EBS, ወዘተ ሚዲያዎች ዓመታዊ በጀታቸው ከፍያለ፣ ካሜራዎቻቸው ውድ፣ የሰው ኃይላቸው ብዙ፣ ከማስታወቂያ ገቢ ያገኛሉ። የሠራተኞቻቸው ደሞዝ የማይቀመስ ነው።

"…ወደ እኔ ወደ ዘመዴ ስቱዲዮ ስንመጣ ግን ወፍ የለም። የስቱዲዮ ካሜራ፣ መብራት፣ ኮምፒዩተር፣ ኤዲተር፣ ዳይሬክተር፣ ሹፌር፣ ጸሐፊ፣ አርታኢ፣ በጀት፣ ደሞዝ፣ ቦነስ ብሎ ነገር የለም። እንደ ሶምሶን ብቻህን ትቆማለህ እግዚአብሔርን ይዘህ ግን ሺ ዉን በአህያ መንጋጋ።

• ጌዴዎናዊነት ደ አሸናፊነት ነው።

"…እንደ አማሪካው FOX ተለቭዥን ጣቢያ ያለ ተቋም መገንባት፣ በ300 የጌድዮን ሠራዊት ብቻ ምድያማውያንን ማሸነፍ ይቻላል። አንተ ፈቃደኛ፣ ታዛዥ፣ ከእውነት የተጣበቅህ ሁን እንጂ እግዚአብሔር ልሥራብህ ካለ አለ ነው አንዱን አንተ ብዙ አድርጎ ይሠራብሃል።

• አይደለም እንዴ…?


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
“…የምነግራችሁ ገና ብዙ አለኝ…” ዮሐ 16፥12 “…ክፉውን ከመካከላችሁ አውጡት።” 1ኛ ቆሮ 5፥13

• እንደምን አደራችሁ?
• እንደምን አረፈዳችሁ?
• እንደምን ዋላችሁ?
• እንደምን አመሻችሁ?

• መልሱ እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
መልካም…

"…አሁን ደግሞ ይሄን 17 ሺ ሰው አንብቦት 34 ፍሬ ሁለት ደርዘን ተኩል ነጠላ ሰዎች ጓ 😡 ብው ብለው የበሰጩበትን ከትላንት ያደረ ርእሰ አንቀጽ ወደ መተቸቱ እናመራለን። በጨዋ ደንብ ነው ታዲያ።

"…ጎጃም ገባሁ ስል የነበረው የተሳዳቢ ብዛት አሁን የለም። በጣም ነው የቀነሰው። በፔጄ ላይ መጠየቅ፣ መመካከር፣ መወያየት፣ በጨዋ ደንብ ከርእሱ ጋር በተገናኘ መወያየት እንጂ አፍላፊ መናገር ያስቀስፋል።

"…በፔጄ ላይ ዘሎ ገብቶ ዐማሮች እዚህ ፔጅ ላይ ምንትሠራላችሁ ሲል ቀስፌ ድራሹን አጠፋዋለሁ። ይሁነኝ ብዬ እያጸዳው ያለሁትን የፔጄን ጽዳት እያየ ዘመዴ የተከታታዮችህ ቁጥር ቀነሰ እኮ ብሎ ዘው ብሎ የሚመጣውንም ቀስፌ ለምን እንደሚቀንስ ከሚስቱና ከባሏ ጋር፣ ከማኅበርተኞቿና ከጓደኞቿ ጋር እንድታወራ አደርጋታለሁ። ይኸው ነው።

"…በርእሰ አንቀጹ ላይ ብቻ እናውራ። በጎጃም ብዙ ለውጥ አለ። አቁሙ ያልኩትን በቲክቶክ ሁላ ከሞጣ ቀራኒዮ ጋር ጌም የሚጫወቱ ፌዘኞች መከልከላቸው ደብዳቤ ወጥቶ አይቻለሁ። ይሄ በአስረስ ላይ፣ በጥላሁን አበጀ ላይ የሠራል ወይ የሚለውን አብረን እናያለን። እንዲያውም ምሥራቅ ጎጃምን ለብአዴን አስረክቦ ምዕራብ ጎጃም የተደበቀው ግንቦቴ ጥላሁን አበጀ የጎጃሙን ሰበር ዜና ትቶ ወለጋ ያለውን ዐማራ ለማስፈጀት ከተደበቀበት ጎጃም ሆኖ ወለጋ ባለው ዐማራ ላይ ሴራ መሥራቱን ተያይዞታል። መጀመሪያ የራስህን መንደር፣ ቀበሌ፣ ሰፈር እስቲ ነፃ አውጣ። ሰፈር ቀበሌህን ለሚሊሻ አስረክበህ ፈርጥጠህ ስታበቃ ጊቤን ተሻግረህ ስለወለጋ መለፈፉ ሼም ኖ።

"…ጌዴዎናዊነት አሸናፊነት ነው። እውነትን፣ ሃቅን ውደዱ፣ እውነት ራሱ እግዚአብሔር እኮ ነው። ከሐሰት የሚገኝ ትርፍ ሞትና ውርደት ብቻ ነው።

• 1…2…3 ጀምሩ… ✍✍✍


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
👆⑥ ✍✍✍ …ዘግተናል ካሉኝ በኋላ፣ ምነው ጭራሽ ስለ እኔ ከበፊቱ በበለጠ ረጃጅም መጣጥፍ መገለጥ ጀመሩ?፣ በእኔ ዙሪያ በቀን እያወጡ ያሉት የምርመራ ወረቀት እኮ የሦስት ተመራቂ ተማሪዎች የመመረቂያ ጽሑፍ የሚወጣው ነው። አትረባም ብለውኝ ሲያበቁ፣ አንባቢም አድማጭም የለውም ካሉኝ በኋላ፣ ይሄን ያህል በእኔ ዙሪያ መቸክቸክና ሲለፈልፉ መዋል ከየት የመጣ ነው? እኔ በበኩሌ ከዚህ የተረዳሁት፣ በመረጃ ቲቪ በሳምንት ሦስት አራት ሰዓት ብቻ በነበረኝ ሳምንታዊ ነጭ ነጯን ከዘመዴ ጋር መርሀ ግብሬ እፈጥር የነበረው ርደተ መሬት፣ ዛሬ መረጃ ቲቪን ለቅቄ በቴሌግራም ብቻ መከሰት ከጀመርኩ በኋላ ሁለት እጥፍ የሆነ የመሬት መንቀጥቀጠረ መፍጠር መቻሌን ነው። በመረጃ ቲቪ ላይ ሳለህ ከነበረኝ infulence ይለዋል ሱሬ። ከዚያ በላይ ነው ዛሬ ካለ መረጃ ቲቪ በቴሌግራም ጦማር  ብቻ ያለኝ influence የላቀ እንደሆነ የተረዳሁት። ማሳያውም ቲቪውን ከመልቀቄ በፊትና ከለቀቅሁ በኋላ የምሰጣቸው አጀንዳዎች ምን ያህል በሶሻል ሚዲያው መንደር አነጋጋሪ እንደሆነ ማመሳከሩ ብቻ በቂ ነው።

"…የዐማራ ፋኖ በጎጃሙ አስረስ መዓረይ አይተችብን የሚሉት የአክቲቪስት ግሪሳው መንጋ ስለእኔ እየፖሰቱ ያሉትን ተራ ተረታ ተረቶች ሰው ሁሉ "ስለ ልጥፉ እኮ ዘመድኩን ከዚህ በፊት አስረድቷል፣ ምናለ ባታደነቁሩን" እያላቸው ሳይ እደመማለሁ። ከዚህ በፊት ስለ አስረስ መዓረይ በመልካም የለጠፍኩትን፣ እየመዘዙ እያመጡ ይሄው የዛኔ አስረስን እንዲህ አድንቆት ነበር፣ አሁን ሌላው ሲከፍለው ዞረበት ሲሉ፣ ሰው ሁሉ በኮሜንት፣ እየገባ "ዘመድኩን እኮ ነግሮሃል፣ ጥሩ ስትሠራ ትመሰገናለህ፣ መጥፎ የሠራህ ጊዜ በጭቃ ጅራፌ ትዠለጣለህ ብሎሃል። ጥሩ ሲሰሩ በጥሩ ያወሳበትን ፖስት እዚህ በማምጣት እባካችሁ ራሳችሁን አታስገምቱ ሲላቸው እያተሁም በሰዉ ንቃተ ኅሊና ማደግ አምላኬንም አመሰግነዋለሁ። እግዚአብሔር ሆይ ዐማራ እንዲነቃ ስላደረግክልኝ፣ ከጥልቅ እንቅልፉ እንዲነቃ ስላደረክልኝ፣ በማንም መደዴ የማይታለክ፣ በሰበር ዜና ውሸት የማይታለል፣ የማንም መንገደኛ ገንዘቡን በመዋጮ ስም እንዳይግጠው ስላነቃህልኝ አመሰግንህሃለሁ። በእነ አበበ በለው፣ በእነ አልማዝ ባለጭራዋ ከመጋጥ፣ በእነሱም ከመመራት ስለታደግከው አመሰግንህሃለሁ። በእኔ ጉዳይ ተቃዋሚዎቼ ምንም አዲስ ማቴሪያል የላቸውም። በእኔ ዙሪያ ቢያወሩ ያንኑ የፈረደበትን ከበረከት ስምኦን ጋር የተነሳሁትን ፎቶ ነው ቢያመጡ። እሱንም ቢሆን ማምጣቱን አሁንስ ሰለቻቸው። ሰዉ በዚህ ዙሪያ ዘመድኩን ጉዳዩን አስረድቶናል ስለሚላቸው እየተዉት ነው የመጡት። እኔ በበኩሌ ከገመትኩት በላይ ግሪሳ የሚባለው ሁሉ የእኔ አንባቢ ከመሆኑም በላይ ያነበበውን የማይረሳ ጭምር ነው ሆኖ ያተሁት። ስለ እኔ በኔጌቲቭ የተለጠፈ ኮሜንት ስር 👎 ነው በየዲስከሽን ፎረሙ እየተሰጠ የማየው። ስለዚህ አገው ሸኔም፣ ኦሮሙማም፣ ስኳዶችም አትችሉኝም። ሲነኩኝ ይብስብኛል።

"…ያስያዝኩት ሱባኤ እንዳለቀ ቦርድ አቋቁማለሁ። የአይቲ ባለሙያዎችን ቡድን አቋቁማለሁ። ከዚያ ደፋር፣ ነጭነጯን ብቻ የሚወራበት ነቃሽ፣ ተቺ፣ እሰጨናቂ፣ ኮሶ ሻጭ የሆነ የቴሌቭዥን ጣቢያ አቋቁማለሁ። በይፋ ነው የማቋቁመው። የራሴን ሰዎች ይዤ ነው የማቋቁመው። በባለቤትነት የምመራው፣ ግርማ ካሣ የማያዘኝ፣ የማያስፈራራኝ፣ ሌሎች ወዳጆቼ የማይጨነቁበትን ጣቢያ ነው የማቋቁመው። ሚልዮን ሳይሆን ጥቂት 300 የጌድዮን ሠራዊት የሆነ አባል ይዤ ነው ወደፊት የምፈነጠረው። ለዚህ ደግሞ የጎጃሙን አገው ሸኔና ግርማ ካሣን በእጅጉ አመሰግናቸዋለሁ። እስከ አሁን መረጃ ቲቪ ላይ ብቆይ ኖሮ እገሌ ቅር ይለው ይሆን ምናምን እያልኩ እንደ ልቤ አልንቀሳቀስም ነበር። አሁን ግን ነፃ ነኝ። በነፃነትም "የእግዚአብሔርና የጌዴዎን ሰይፍ" እያልኩ እየጮህኩ እገጥማቸዋለሁ።

"…ታዘቡኝ። እኔ ጎጃም ከገባሁ በኋላ በጎጃም ምን ታዘባችሁ? መሰደቤን፣ መወገሬን፣ በእነ አገው ሸኔ መዋረዴን አትዩ። አትመልከቱ። ከመረጃ ቲቪ በገዛ ፈቃዴ ማገልገል ማቋረጤንም አትመልከቱ። እንደው በሞቴ፣ በሳንቃው ደረቴ ምን ታዘባችሁ? ያ ሁላ ሰበር ዜና የት ገባ? …ተዉ ጦር ሜዳ ነው ያላችሁት ቲክቶክ አትጠቀሙ ብዬ ስጮህ፣ መዓረይ እና ጥላሁን አበጀ 24/7 በልዩ ፈቃድ ፌስቡክ ላይ ተጥደው ሲውሉ፣ እንደ ተቋም መረጃ በአንድ ማዕከል ብቻ ይፍሰስ ብዬ ያልኩትን ዛሬ በማርሸት ፀሐዩ ፊርማ እኔ የጮህኩበትን ጉዳይ ይፋ አላወጡትም? ብዙ ሰው እየጠየቀኝ ነው። ዘመዴ አንተ ጎጃም ገባሁ ካልክ ጊዜ ጀምሮ በጎጃም ጦርነት ቆሟል እንዴ? ሠራዊቱ ተበተነ ወይስ ምንድነው ዝም ጭጭ ያለው ነገር? ሰበር ዜና የጠረረበት ሙሉጌታ አንበርብር ብቻ እኮ ነው አሁን በጎጃም ጧ ያለችን አንዲት ጥይት ሰበር እያለ መዘገብ የጀመረው። ሙሌ እነ ደረጄ በላይን በጠቅላይ ግዛቱ ስም መግለጫ እንዲያወጣ ማድረጉን እንደ ጀብዱ ቆጥረውለት ስኳዶች ማስገን መጀመራቸውና በጎጃም እንደ በፊቱ በዞንና በወረዳ ከተሞች ውስጥ ውጊያ ያለመኖሩ ምክንያቱ ምንድነው እያሉኝም ነው። የሙሉን ጉዳይ እስቲ እጠይቀዋለሁ። በዚህ ዓይነት እነ ሀብቴም ወደ እነ ባዬ በእነ ሙሌ ምክር ገብተው ይሆን እንዴ ብዬ እንድጠረጥር ነው ያደረገኝ። እነ እስክንድር ነጋ ድርድር ሲሉ፣ እነ አስረስ መዓረይም ድርድር ሲሉ፣ እነ ማርሸትም ኦሮሙማው በዐማራ ላይ የዘር ማጥፋት አልፈጸመም ሲሉ። በዚያ ላይ አስረስና አመራሩ የጎጃምን ፋኖ ሽባ አድርገው ከዞንና ከተሞች አስወጥተው፣ ቢኖሩም እንዳይዋጉ ለአገዛዙ ሠራዊት ቦታ እንዲለቀቅ አድርገው፣ አቢይ አህመድ 1ሺ ዓመት ቢዋጉን አያሸንፉንም ብሎ እንዲኩራራ አድርገውታል። ኧረ ምን እየሆነ ነው ጎጃም እያሉ ነው ብዙዎች። የአገዛዙ ጦር ቀበሌና ጎጦች ውስጥ ነው አሁን የሚዋጋው። ከከተማ፣ ከዞን ከወረዳ የተባረረው የዐማራ ፋኖ በጎጃም አሁን ከቀበሌና ጎጥ ካስወጡት የት ልሄድ ነው? ይሄንን የአገዛዙ ጦር ቀበሌ መውረዱን ነው እነ ሙሉጌታ አንበርብር ሰበር እያሉ በመዘገብ ላይ ያሉት። በሌላ አባባል የአገዛዙን ድል ነው እየዘገቡ ያለው ማለት ነው። በጣም ያሳዝናል በጣም የሚሉ መተርጉማንም አሉ። ምርር ብሎ ጎጃሜ በሜካፕ ተሽሞንሙኖ የደላው መስሎ ከመታየት ወጥቶ፣ ህመሙንም በግላጭ ተናግሮ መፍትሄ ቢፈልግ ነው የሚሻለው። አሁን በጫካ ውስጥ ውብ ፎቶና በውሸት ሰበር ዜና፣ በእነ ደመሰስናቸው፣ ፈጀናቸው ማንንም ማጃጃል የማይቻልበት ዘመን ላይ ተደርሷል። ለእነ ፎግረህ፣ ዋሽተህ፣ ቀጥፈህ ብላዎች፣ በሰው ደም ነጋዴዎች፣ ኡጋንዳ፣ ባህርዳርና አዲስ አበባ ቢዝነስና ቪላ አጧጧፊዎች ይሄ የእኔ መራር እውነት ይጎረብጣቸዋል። መፍትሄው ይመራል ግን ዋጠው፣ ተጋተው ትፈወሳለህ ብቻ ነው። ከራስ አልፎ ሕዝብን ማስተርቤት ማድረግ ኃጢአት ነው። ያን ጡርንባ እየነፋ ጠላቱን ድባቅ ይመታ የነበረው ጀግና የሕዝብ ማዕበል በጎጃም ዳግም ካልተፈጠረ በእነ መዓረይና በእነ ፓስተር ዳዊት ትግል ጎጃም አያሸንፍም። ተናግሬአለሁ። ይመዝገብልኝ። 

• ነገ እሁድ ምሽት ልክ በ12 ሰዓት በድሮው በመረጃ ቲቪ ሰዓቴ በቲክቶካችን ላይ እንገናኛለን። የነገ ሰው ይበለን። ቆይቼ የአስተያየት መስጫ ሳጥኑን እከፍትላችኋለሁ። መልካም ቆይታ።

• ድል ለዐማራ ፋኖ…!
• ድል ለተገፋው ለዐማራ ሕዝብ…!

~ • ይደፈርሳል… ግን ደግሞ ይጠራል…✊

•••

ሻሎም…!  ሰላም…!

ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
አሸበርቲው/አስነቀልቲው
ጥር 17/2017 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ።


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
👆⑤ ✍✍✍ "…ለምን እንደማታሸንፉኝ ልንገራችሁ። እውነት የላችሁም።  በፋኖ ጉዳይ ላይ ዕውቀትም የላችሁም። መንጋ ናችሁ። የፋብሪካ ዕቃ ናችሁ። ማሽን የሚያሽከረክራችሁ ምስኪን ቁሶች ስለሆናችሁ ነው የምትቃወሙኝ። የማታሸንፉኝም ለዚያ ነው። ቀጣይነት፣ ትእግስ፣ ዕውቀት፣ እምነት የላችሁም። እኔን የሰሙ፣ ከእኔ ጋር የመከሩ፣ ገና ድሮ ነገሩ የገባቸው ግን ከእኔ ጋር ናቸው። ጉዳዩ መንፈሳዊ ጦርነት መሆኑ የገባቸው ከእኔ ጋር ናቸው። አራት ኪሎን፣ ሥልጣን፣ ሀብትና ዝናን የሚፈልጉ፣ እሱን ብቻ ብለው የሚንቀሳቀሱ ግን ቅርብ አዳሪዎች ናቸው። ነገርየው ከዚያ በላይ እጅግ የረቀቀ ነው። ጥቂት ልባሞች የሚመሩት ባይሆን ኖሮ በእነ አስረስ መዓረይ፣ በእነ እስክንድር ነጋና በኮተታም አዝማሪዎች የሚመራው ቢሆን ገና ድሮ ተፈጽመን ነበር። ትግሉ በአስተማማኝ ልባሞች እጅ ስለተያዘ ነው በባዶ እጅ ተጀምሮ ከዚህ የደረሰው። እኔን የማታሸንፉኝም ለዚያ ነው። ሩቅ ሆኜ፣ የረቀቀውን በቅርብ እንዳለ እንዳይ እንድመለከት ያደረገኝ ኃይል ባይኖር ኖሮ ታሸንፉኝ ነበር። ሥልጣን፣ ገንዘብና ዝና አልፈልግም፣ ትግሉም ፍጻሜ ሲያገኝ ከአንድ ቀን ዞር ብዬ አላየውም እያልኩ እየጮህኩ፣ እየማልኩ እየተገዘትኩም ምድረ የፖለቲካው ቅማንት የትግሬ ዲቃላው ስኳድ፣ ምድረ የፖለቲካው አገው ሸንጎ ሸኔው ቅባታም መናፍቅና ወሃቢያም ሁላ ዝም ብለህ አፍህን ትከፍትብኛለህ። ነገር ግን አታስቆሙኝም። አታሸንፉኝምም።

"…ትንተናውን አቁሜ ታሪኩን ብቻ በማንበብ የጀመርኩትን ለመፈጸም እንቀጥል። በዚያም ሌሊት እግዚአብሔር፡—በእጅህ አሳልፌ ሰጥቻቸዋለሁና ተነሥተህ ወደ ሰፈር ውረድ። አንተም ለመውረድ ብትፈራ አንተ ከሎሌህ ከፉራ ጋር ወደ ሰፈሩ ውረድ፤ የሚናገሩትንም ትሰማለህ፤ ከዚያም በኋላ ወደ ሰፈሩ ትወርድ ዘንድ እጅህ ትበረታለች፡ አለው። እርሱና ሎሌው ፉራ በሰፈሩ ዳርቻ ወደ ነበሩት ሰልፈኞች ወረዱ። ብዛታቸውም እንደ አንበጣ የሆነ ምድያማውያንና አማሌቃውያን የምሥራቅም ሰዎች ሁሉ በሸለቆው ውስጥ ሰፍረው ነበር፤ የግመሎቻቸውም ብዛት ቍጥር እንደ ሌለው በባሕር ዳር እንዳለ አሸዋ ነበረ። ጌዴዎንም በደረሰ ጊዜ አንድ ሰው ሕልምን ለባልንጀራው ሲያጫውት፡— እነሆ፥ ሕልም አለምሁ፤ እነሆም፥ አንዲት የገብስ እንጎቻ ወደ ምድያም ሰፈር ተንከባልላ ወረደች፥ ወደ ድንኳኑም ደርሳ እስኪወድቅ ድረስ መታችው፥ ገለበጠችውም፥ ድንኳኑም ተጋደመ ይል ነበር። ባልንጀራውም መልሶ፡— ይህ ነገር ከእስራኤል ሰው ከኢዮአስ ልጅ ከጌዴዎን ሰይፍ በቀር ሌላ አይደለም፤ እግዚአብሔር ምድያምንና ሠራዊቱን ሁሉ በእጁ አሳልፎ ሰጥቶአል፡ አለው።

"…ጌዴዎንም ሕልሙንና ትርጓሜውን በሰማ ጊዜ ሰገደ፤ ወደ እስራኤልም ሰፈር ተመልሶ፡— እግዚአብሔር የምድያምን ሠራዊት በእጃችሁ አሳልፎ ሰጥቶአልና ተነሡ፡ አለ። ሦስቱንም መቶ ሰዎች በሦስት ወገን ከፈላቸው፥ በሁሉም እጅ ቀንደ መለከትና ባዶ ማሰሮ፥ በማሰሮውም ውስጥ ችቦ ሰጠ። እርሱም፡— እኔን ተመልከቱ፥ እንዲሁም አድርጉ፤ እነሆም፥ ወደ ሰፈሩ ዳርቻ በደረስሁ ጊዜ እኔ እንደማደርግ እንዲሁ እናንተ አድርጉ፤ እኔ ከእኔም ጋር ያሉት ሁሉ ቀንደ መለከት ስንነፋ፥ እናንተ ደግሞ በሰፈሩ ዙሪያ ሁሉ ቀንደ መለከታችሁን ንፉ፡— ለእግዚአብሔርና ለጌዴዎን፥ በሉ፡ አላቸው። ጌዴዎንም ከእርሱም ጋር የነበሩት መቶ ሰዎች በመካከለኛው ትጋት ትጋቱም በተጀመረ ጊዜ ወደ ሰፈሩ ዳርቻ መጡ፤ ቀንደ መለከቶችንም ነፉ፥ በእጃቸውም የነበሩትን ማሰሮች ሰባበሩ። ሦስቱም ወገኖች ቀንደ መለከቶችን ነፉ፥ ማሰሮችንም ሰበሩ፥ በግራ እጃቸውም ችቦችን፥ በቀኝ እጃቸውም ቀንደ መለከቶችን ይዘው እየነፉ፡— የእግዚአብሔርና የጌዴዎን ሰይፍ፡ ብለው ጮኹ።

"…ሁሉም በየቦታው በሰፈሩ ዙሪያ ቆመ፤ ሠራዊቱም ሁሉ ሮጠ፥ ጮኸ፥ ሸሸም። ሦስቱንም መቶ ቀንደ መለከቶች ነፉ፥ እግዚአብሔርም የሰውን ሁሉ ሰይፍ በባልንጀራውና በሠራዊቱ ሁሉ ላይ አደረገ፤ ሠራዊቱም በጽሬራ በኩል እስከ ቤትሺጣ ድረስ በጠባት አጠገብ እስካለው እስከ አቤልምሖላ ዳርቻ ድረስ ሸሸ። የእስራኤልም ሰዎች ከንፍታሌምና ከአሴር ከምናሴም ሁሉ ተሰብስበው ምድያምን አሳደዱ። ጌዴዎንም፡— ምድያምን ለመገናኘት ውረዱ፥ እስከ ቤትባራም ድረስ ያለውን ውኃ፥ ዮርዳኖስን፥ ያዙባቸው ብሎ መልክተኞችን በኤፍሬም ወዳለው ተራራማ አገር ሁሉ ሰደደ። የኤፍሬም ሰዎችም ሁሉ ተሰብስበው እስከ ቤትባራ ድረስ ውኃውን፥ ዮርዳኖስን፥ ያዙ። የምድያምን ሁለቱን መኳንንት ሔሬብንና ዜብን ያዙ፤ ሔሬብንም በሔሬብ ዓለት አጠገብ ገደሉት፥ ዜብንም በዜብ መጥመቂያ ላይ ገደሉት፤ ምድያምንም አሳደዱ፥ የሔሬብንና የዜብንም ራስ ይዘው ወደ ዮርዳኖስ ማዶ ወደ ጌዴዎን መጡ። አለቀ። በ300 ሰው ጌዴዎን አሸነፈ። ሠራዊቱም "የእግዚአብሔርና የጌዴዎን ሰይፍ" ብሎ ፎክሮ አሸነፈ። እግዚአብሔርም ታማኝነቱን፣ ጌዴዎንም አማኝነቱን፣ ሁለቱም ቃሊኪዳናቸውን ጠበቁ። እግዚአብሔር መቼም እግዚአብሔር ነው። ጌዴዎን ግን ሙሉ በሙሉ እግዚአብሔርን አምኖ፣ የታዘዘውን ሁሉ ሳያቅማማ፣ ያለአንዳች መጠራጠር አምኖ ተቀብሎ፣ "ከፈራህ" በእጅህ አሳልፌ ሰጥቻቸዋለሁና ተነሥተህ ወደ ሰፈር ውረድ። አንተም ለመውረድ ብትፈራ አንተ ከሎሌህ ከፉራ ጋር ወደ ሰፈሩ ውረድ" እያለውም። አይ አንተን ይዤ አልፈራም በማለት በእምነቱ ጸንቶ አሸነፈ።

"…ሁል ጊዜ የምላችሁ ነው። ማሸነፍ በብዛት አይደለም በጥራት እንጂ። መታበይ አይደለም፣ ውዳሴ ከንቱም ፈልጌም አይደለም። ስለ እውነት እንነጋገር ከተባለ ከዐማራ ወገን ልክ እንደ እኔ እንደ ጃል ቆቱ ወዲ አስገዶም ዓይነት ያለ አንድ አስር ቁርጠኛ ባለማዕተብ ፅኑ፣ ቀጣይነት ያለው ሥራ የሚሠሩ፣ ያለ ጥቅም በትርፍ ጊዜ ሳይሆን እንደ ሥራ ቆጥረው ለዐማራ የሚታገሉ፣ ስድብን፣ ዛቻን ሳይፈሩ ታግሰው የሚሠሩ ቆራጥ ዐማሮች ቢኖሩ ኖሮ ዐማራው የት በደረሰ ነበር። እንደ ዕድል ሆኖ ግን ዐማራው በዚህ አልታደለም። ሆዳም ይበዛዋል። ጎንደሬ ከሆነ ዐማርኛ በሚናገር፣ እዚያው ጎንደር በተወለደ በፖለቲካው ቅማንት በትግሬ ዲቃላ የተወረረ ነው። ጎጃሜ ከሆነም እንደዚያው ነው። አማርኛ በሚናገር በፖለቲካው አገው ሸንጎ የተጠረነፈ ነው። ዐማራው በጎጃምም በጎንደርም የፖለቲካው ውክልና፣ የኢኮኖሚው፣ የቢሮክራሲው፣ የፍትሕና የጸጥታው ተቋማት በሙሉ የተያዙት በእነዚህ ዐማርኛ በሚናገሩ ፀረ ዐማራ ኃይሎች ነው። አክቲቪዝሙ፣ ጋዜጠኝነቱ ሳይቀር የተወረረው በእነዚህ ፀረ ዐማራ ኃይሎች ነው። ዐማራ ትልቁ ጉዳቱ አማርኛ በሚናገር ሌላ አካል ተወርሮ መያዙ፣ መረገጡ ነው። እናም ይሄ ደግሞ ቀስ እያለ እየጠራ ነው የሚመጣው። ለምሳሌ ያ መሸጦ ጠቋር ልቡሰ ሥጋ ጋኔል የመሰለው አማኑኤል አብነት ምኑ ነው ዐማራ የሚመስለው? ከእሱም ብሶ ደግሞ እኮ "ከዘመድኩን ጋር የሚገናኝ ዐማራ ጥቁር ውሻ ይውለድ" ብሎ ይራገማል። ጉድ እኮ ነው።

"…እናም ሲጠቃለል እኔ ብቻዬን 300 ወደዳጆቼን ይዤ ድብን አድርጌ ይሄን የአየር ላይ መንጋ ግሪሳ አጸዳዋለሁ። አሸንፈዋለሁም። ስለእኔ እየቸከቸኩ እንዲኖሩ፣ እንዲዋረዱ፣ እንዲቀልሉ አደርጋቸዋለሁ። እኔን የማልደመጥ፣ የማልረባ ከሆነ፣ በጎጃም መሬት ላይ አንድም ነገር መለወጥ የማልችል መደዴ ከሆንኩ፣  ታዲያ ምነው 24 ሰዓት ስለ እኔ ሲጽፉ፣ ሲቸከችኩ፣ በቲክቶክ ሲበጠረቁ ይውላሉ? ዘመዴ ያመዋል፣ እብድ ነው፣ ቀውስ ነው፣ ማይም ነው፣ ክንፉን ሰብረነዋል፣ ከአሁን በኋላ ያለውን ቢል ብቻውን ቀርቷልና አንመለስበትም፣ በእሱ ጉዳይ ጨርሰናል፣ ፋይላችንንም…👇⑤ ✍✍✍


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
👆④ ✍✍✍ …የፈጠረበት የአቶ ግርማ ካሣና መሬት ላይ በፋኖ ውስጥ የተሰገሰጉት ፓስተሮች የጠበቀ ግኑኝነት ምክንያት ነው። ጴንጤዎች የዐማራ ፋኖን ትግል በጸሎት፣ በገንዘብ፣ በሞራል መርዳት ይችላሉ። ነገር ግን ዶሮ አርዶ መብላት ኃጢአት ነው የሚል እምነት እያራመደ የሚኖር ጴንጤ ጠላት የተባለ ሰው ገድሎ አያሸንፍም እና ከትግሉ በአስቸኳይ መውጣት አለባቸው። የተገደለ፣ የታረደ የበሬ፣ የበግ፣ የዶሮና የፍየል ሥጋ የሚበላው ጴንጤ፣ ዶሮም በግም ለማረድ ከጎረቤት አራጅ የሚጠራ ጴንጤ የዐማራ ፋኖን ወሳኝ የፖለቲካ ቁልፍ ቦታ ይዞ ኦርቶዶክሳቅያኑን ጀግኖች፣ ሙስሊሞቹን ጀግና የዐማራ ልጆች እያስገደሉ መኖር የለባቸውምና በአስቸኳይ ከትግሉ ገለል እንዲሉ በአክብሮት እጠይቃለሁ። እንደ ውሻ ውኃ የጠጡ 9,700 ሠራዊት ሲመለስ የቀረው 300 ሠራዊት ብቻ ነው።

"…እግዚአብሔርም ጌዴዎንን፡— በእጃቸው ውኃ በጠጡት በሦስት መቶ ሰዎች አድናችኋለሁ፥ ምድያማውያንንም በእጅህ አሳልፌ እሰጥሃለሁ፤ የቀሩት ሕዝብ ሁሉ ግን ወደ ስፍራቸው ይመለሱ፡ አለው። የሕዝቡንም ስንቅና ቀንደ መለከት በእጃቸው ወሰዱ፤ የቀሩትንም የእስራኤል ሰዎች ሁሉ ወደ ድንኳናቸው ሰደዳቸው፥ ሦስቱን መቶ ሰዎች ግን በእርሱ ዘንድ ጠበቃቸው፤ የምድያምም ሰፈር ከእርሱ በታች በሸለቆው ውስጥ ነበረ።" ይለናል መጽሐፍ ቅዱስ። "…በሦስት መቶ ሰዎች አድናችኋለሁ፥" ከ32 ሺ ሰው መሃል 21 ሺ ፈሪ፣ ድንጉጥ፣ ቅዘናም፣ ሽንታም ተቀንሶ፣ ከዚያም ከቀሩት 10 ሺዎች መካከልም የውሻ ጠባይ ያላቸው 9,700 ሰዎች ተቀንሰው፣ በአጠቃላይ ከ32 ሺ ሰው 31,700 ሰው ተቀንሶ 300 ሰው ብቻ በእግዚአብሔር ተመረጠ። ደስ አይልም በማርያም። እስቲ እዚህም ጋር ንባቡን ቆም አድርገው አካባቢዎ ጋር ሰው የማይረብሹ ከሆነ በእልልታ እልልልል ብለው፣ ወይም በጭብጨባ፣ አልያም አንድ አባታችን ሆይ ጸልየው እግዚአብሔርን አመስግነው ጦማሩን ማንበብዎን ይቀጥሉ። መታመን ለራስ ነው። ያድርጉት። አካባቢው ላይ ሰው የሚረብሹ ከሆነ በልብዎ እልልል ይበሉ። ይጸልዩ። እግዚአብሔር ሆይ ክበር ተመስገን ይበሉ። በማርያም። አመሰግናለሁ።

"…በሦስት መቶ ሰዎች አድናችኋለሁ፥ በቃ እግዚአብሔር ካለ አለ ነው። በሦስት መቶ ሰዎች አድናችኋለሁ፥ አዛዡ፣ ድልአድራጊው እግዚአብሔር ነዋ እንዲህ ያለው። እንደ ምድር አሸዋ፣ እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛውን የጠላት ጦር እኔ እሰብርላችኋለሁ። ምድያማውያንንም በእጅህ አሳልፌ እሰጥሃለሁ አለው የእኛ ጌታ፣ የእኛ አምላክ። ደስ አይልም በማርያም "ምድያማውያንንም በእጅህ አሳልፌ እሰጥሃለሁ" አየህ አሁን እስራኤል ሊጎርር፣ ሊኩራራ አይችልም። 32 ሺ ሆነን ወጥተን ገጥመናቸው በኃይላችን፣ በክንዳችን አሸነፍን ማለት አይችልም። በ300 ሰው ሚልዮን ሠራዊት ካሸነፍክ፣ ያውም ስንዴ ሲወቃ የተገኘ ወጣት እየመራው፣ በየትኛውም ውጊያ ተሳትፎም መርቶም በማያውቅ ሰው እየተመራ፣ በእጁ የስንዴ መውቂያ ዱላ የያዘው ጌዴዎን እየመራው 300 ሰው ካሸነፈ ሌላ ምንም ሊባል አይችልም። ክብሩን ሁሉ ጠቅልሎ የሚወስደው እግዚአብሔር ብቻ ነው። ደግሞም እግዚአብሔር ሕዝቡን ቀንስ ሲለው የነገረውም ይሄንኑ ነው። እግዚአብሔርም ጌዴዎንን፡— ከአንተ ጋር ያለው ሕዝብ በዝቶአል፤ ስለዚህ እስራኤል፡— እጄ አዳነኝ ብሎ እንዳይታበይብኝ እኔ ምድያምን በእጃቸው አሳልፌ አልሰጣቸውም እናም 32 ሺ ሕዝብ ብዙ ነውና ቀንስ ነበር ያለው። እጄ አዳነኝ ብሎ እንዳይታበይብኝ። መዝግቡት።

"…አሜሪካ እንዳይከፋት፣ በሩሲያ ኦርቶዶክስ ዓይን እንዳታየን ፋኖዎች መስቀል ማንጠልጠል፣ ዳዊት መሸከም አቁሙ ከተባሉ ቆዩ። አርበኛ ዘመነ ካሴ ራሱ ቀንሣል፣ እነ ጌታ አስራደ ጭራሽ የላቸውም፣ እነ መዓረይ የሉበትም። ሰው እምነቱን ሊደብቅ አይችልም። አይገባውምም። የኢራቅ ኦርቶዶክሳውያን እኮ በቃ ሊጠፋ ሲሉ ነው ተደራጅተው ዛሬ ራሳቸውን ያስከበሩት። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳውያንና በወለጋ የጸዱት የወሎ እስላም ዐማሮች ተደራጅተው ራሳቸውን ከሚያርዳቸው የብልፅግና ወንጌልና ከአክራሪ ፅንፈኛ የኦሮሞ የወሃቢይ እስላም መንግሥት ራሳቸውን ቢታደጉ ምን ነውር አለባቸው? ምንም ነውር አይደለም። ነገር ግን ፓስተሮቹ የፋኖ አመራሮች ናቸው ይሄንን እያስኬዱ ያሉት። ከውስጥና ከውጭ ተረባረቡብኝ እኮ። እስቲ አብዛኛው እኔን የሚሰድቡ ቲክቶከሮች፣ ዩቱዩበሮች፣ አክቲቪስቶችን ተመልከቱ የሚበዙቱ ጴንጤዎችና የወሃቢያ እስላሞች ናቸው። መሀመድ ሀሰን የተባለ እስላም ዐማራ መሳይ አሞራ ሁሌ የሚዘበዝበኝ በእምነት የተያያዘ ዘጀንዳ ስላለው ነው። እንጂ እኔ ዘሬን የት አባቱ ቆጥሮት ነው እሱ ዐማራ እኔን ጋላ የሚያደርገው? እኔ ቆቱ ነኝ እንጂ ጋላ ነኝ፣ ኦሮሞ ነኝ፣ ትግሬ ዐማራ ነኝ አላልኩ። ጉራጌ ሲዳማ ወላይታ ነኝም አላልኩ። ከመሬት ተነሥቶ በአፉ ሲቀዝን ሳይ እኔ ለእሱ አፍራለሁ። በዐማራ ጉዳይ ከጫማዬ ስር በታች እንኳ መሆን የማይችሉ ገመድ አፍ ተብታባ ባንዳ የባንዳ ልጆች እኔ ተጯጩሄ ከዚህ ያደረስኩትን የዐማራ ትግል እነሱ በአናት መጥተው አዛዥ ናዛዥ መሆን ይፈልጋሉ። የት አባክ ነበርክ እኔ እንደ ብራቅ ዐማራ ይሰብሰብ፣ ይታጠቅ፣ ይመክት፣ ያነክት እያልኩ ስጮህ የት አባክ ነበርክ። ዛሬ መሳይ መኮንን፣ ደረጄ ሀብተወልድ፣ ፋሲል የእኔዓለም ቂጥ ስር ተወትፈህ የምትልከሰከስ ልክስክስ ዐማራ መሳይ አሞራ ሁላ የትአባክ ነበርክ? እነርሱ ለኦሮሙማ ተገርደው የዐማራን ሞት፣ መፈናቀል፣ ስደት፣ መዘረፍ፣ መታሰር ሲደብቁ ማነው ኢኡ ብሎ ዓለም እንዲያውቅ ያደረገው። በድፍረት እናገራለሁ እኔ ዘመድኩን በቀለ ጃል ቆቱ ወዲ አስገዶም ነኝ። የትአባክ ነበርክ አንት ሆዳም፣ ሽንታም ፈሪ ቦቅቧቃ፣ ሰው መሳይ በሸንጎ። የት ነበርክ አልኩህ። አንት ውለታ ቢስ ዘረ ቆርጥም ድመት ሁላ። የት ነበርክ እኔ አይደለሁ እስከአሁን ሳላወላውል ቀጥ ብዬ የቆምኩት? ወናፍ ወንፊት ሁላ።👇④ ✍✍✍


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
👆③✍✍✍ "…ትእዛዝ ነውና ጌዴዎንም እሺ አምላኬ ታዛዥ ነኝ በማለት "ሕዝቡንም ወደ ውኃ አወረደ። እግዚአብሔርም ጌዴዎንን፡— ውሻ እንደሚጠጣ ውኃ በምላሱ የሚጠጣውን ሁሉ፥ እርሱን ለብቻው አድርገው፤ እንዲሁም ሊጠጣ በጕልበቱ የሚንበረከከውን ሁሉ ለብቻው አድርገው፡ አለው።" ይሄ የስነ ምግባር ፈተና ነው። ወታደር ጨዋ፣ ወታደር ሥነ ሥርዓት ያለው፣ በአለባበሱ፣ በአቋሙ፣ በአካሄዱ ሁሉ የሚቀናበት፣ አረማመዱ፣ አነጋገሩ ሁሉ የሚያስደምም፣ አበላሉ፣ አጠጣጡ ሁሉ ጨዋነት፣ የሀገሩን፣ የሕዝቡን፣ የማኅበረሰቡን ባሕል፣ ሃይማኖት የማይጋፋ መሆን አለበት። ወታደር ሻማ ነው። የሀገር ሻማ፣ እሱ እየበራ፣ እየቀለጠ ለትውልድ የሚኖር። ወታደር ሌባን የሚፀየፍ፣ ሕዝቡን ከውጭ ወራሪ የሚጠብቅ እንቅልፍ አልቦ ዘበኛ ነው። ወታደርት ምርጫም ይጠይቃል። ስትመረጥ ነው በኦጋዴን በረሃ በውኃ ጥም እየተቃጠልቅ፣ በፀሐይ እያረርክ ሀገርና ሕዝብ የምትጠብቀው። ያለምርጫ አይሆንም። ያለምርጫ ወታደር ስትሆን ሌባ ነው የምትሆነው። ሴት ስታይ እንደውሻ መድፈር ነው የሚያምርህ፣ ዝርክርክ፣ ስድ፣ ባለጌ ነው የምትሆነው። ገበሬ የምታርደው፣ የምትገድለው ምርጫው የአባገዳይ የኦሮሙማው ሲሆን ብቻ ነው። እናም ጌዴዎን የሥነ ምግባር ፈተና፣ የዲሲፕሊን ፈተና ወታደሮቹን እንዲፈትን አዘዘው። ወደ ወንዙ ወረዱ። ውኃም ጠጡ አላቸው። ውኃውን ሲያዩ ከመጠማታቸው የተነሣ እንደ ውሻ አጎንብሰው በምላሳቸው፣ በአፋቸው የጠጡትን ለብቻ፣ ደግሞም ምንም ቢጠማቸው ተረጋግተው ሰው ናቸውና እንደ ሰው በእጃቸው ውኃውን ቀድተው የጠጡትን ለብቻ አድርጎ ለየ። መጽሐፍ ቅዱስ ከቀሩት 10 ሺ ወታደሮች መካከል "…በእጃቸውም ውኃ ወደ አፋቸው አድርገው የጠጡት ቍጥር ሦስት መቶ ነበረ፤ የቀሩት ሕዝብ ግን ውኃ ሊጠጡ በጕልበታቸው ተንበረከኩ።" ነው የሚለን። ኢማጂን አለ ዶክሌ ነፍሱን ይማረውና ተመልከቱ 9,700 ሰዎች የውሻ ባሕሪ ተላብሰው ስለተገኙ ከጦር ሜዳው አሰላለፍ ውጪ ተደርገው ሲባረሩ ሰው ሆነው የተገኙት 300 ሰዎች ብቻ ሆነው ተገኙ።

"…ለዚህ ነው ሁልጊዜ ከብዛት ጥራት እያልኩ የምለፍፈው። ለምንድነው የፋኖ ትግል እንዲህ የተተረማመሰው ያልን እንደሆነ ትግሉን፣ ፈሪዎች፣ ድንጉጦችና ውሾች ስለተቀላቀሉት ነው። ገለባ፣ እንክርዳት ቢዘሩት አይጸድቅም፣ ፈሪም ቢያሰልፉት አያሸንፍም። የራሱን ሕዝብ ነፃ ለማውጣት ጫካ ገብቶ ሲያበቃ፣ ከሕዝቡ ስንቅና ትጥቅ እየቀረበለት፣ ያንኑ ሕዝብ መልሶ ሲግጠው፣ ሲዘርፈው፣ ሲሰድበው፣ ሲያዋርደው፣ ሲያግተው ስታይ ይሄ ከውሻም በላይ ነው። ውሻ ነውሯን በአደባባይ ነው የምታሳየው። ውሾች ተራክቦ የሚፈጽሙት በአደባባይ ነው። ነውረኞች ሁሉ እንዲህ ናቸው። አሁንም ከፋኖ ትግል ውስጥ ፈሪዎች፣ ድንጉጦች፣ እና ውሾች በአስቸኳይ መልቀቅ አለባቸው። ጀግኖች፣ የበላይ ዘለቀ፣ የአጼ ቴዎድሮስ፣ የንጉሥ ሚካኤል፣ የአፄ ምኒልክ ልጆች ወደ ፊት መምጣት አለባቸው። ስግብግቦች፣ ነውረኞች፣ ዋሾና ቀጣፊ፣ የልቡን ጣኦት ሳያፈርስ፣ ስሙም ሳይቀየር፣ ብአዴን፣ ወያኔ፣ የሻአቢያ ተላላኪ፣ የኦሮሙማ ገረድ፣ ውሻ ሆኖ ከፋኖ ትግል ውስጥ የገቡ ሁሉ በአስቸኳይ ከፋኖ ትግል መውጣት አለባቸው።

"…ጴንጤ የፋኖን ትግል መንራት አይችልም። የለበትምም። ጴንጤ ፈሪ ነው። ፈሪ ነው ሲባል ፍርሃቱ የሚመነጨው በሃይማኖቱ መመሪያ ምክንያት ነው። ጴንጤ ዶሮ፣ በግ፣ ፍየል፣ በሬና ላም ማረድን ነፍስ እንደ ማጥፋት ነው የሚቆጥረው። ነገር ግን የታረደ የዶሮ ሥጋ የሞተ፣ የተገደለውን እንክት አድርጎ የሚበላ ፍጡር ነው። ጴንጤ ዶሮ የሚያሳርደው ጎረቤቱን ኦርቶዶክሳዊ ጠርቶ ነው። እሱ ጻድቅ ኦርቶዶክሱ ኃጥእ መሆኑ ነው። እናም ጴንጤዎቹ ከፋኖ አመራርነት በተለይ በአስቸኳይ መልቀቅ አለባቸው። ይሄ ደግሞ በጎንደር፣ በሸዋና በጎጃም ፋኖዎች ውስጥ በሰፊው ይንጸባረቃል። በሸዋ በእስክንድር የመከታው ፋኖ ውስጥ ፓስተር ዮናስ አይዋጋም፣ ግን ከመረጃ ቲቪው ፓስተር ግርማ ካሣ መመሪያ እየተቀበለ እነ ደሳለኝና እነ መከታው እንዳይስማሙ እያደረገ የሸዋን ትግል አፈር ከደቼ ያበላዋል። ግርማ ካሣ እነ ደሳለኝን ነፍሱ የምትጸየፈው በሌላ በምንም አይደለም። ዋነኛው ሃይማኖት ነው። አለቀ። ጎንደርም እየበጠበጡ ያሉት እነማን ናቸው ያልን እንደሆነ እነ ጌታአስራደ እና እነ ኢያሱ አባተ ናቸው። ለምን የሚመሩት በፓስተር ምስጋናው አንዷለም ነው። ፓስተር ምስጋናው አንዷለም ፋኖ ለምን ዳዊት ይዞ፣ መስቀል አንጠልጥሎ ይዋጋል? ትክክል አይደለም በማለት ሳይደብቅ በአደባባይ የተናጋረ ሰው ነው። ይኸው ከእስክንድር ጋር ገጥመው የጎንደርን አንድነት እየበጠበጡ ያሉትም እነዚህ ኃይላት ናቸው። ጎጃምም በጴንጤ ፓስተሮች የተሞላ ነው። የጎጃም ዐማራ ፋኖን ሽባ ያደረጉት እነ መዓረይ እና ፓስተሮቹ ናቸው።

"…በተለይ አርበኛ ዘመነ ካሤ ማርያምን፣ እመቤቴን እያለ እየማለ የዐማራ ፋኖ በጎጃምን በብልፅግና ወንጌል አማኞች መሙላቱን አልወደድኩለትም። አባቱ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ የሆነውንና ከአቢይ አሕመድ ጋር እጅግ የቀረበ ግንኙነት ያላቸውን፣ ከአቢይ አህመድም ጋር በአንድ ላይ  የሚጸልዩትን የአቶ መሀሪን ልጅ ያውም የፕሮቴስታንት ወጣቶች ሊግን እንዲመራ በአቢይ ታጭቶ የነበረውንና በምን ምክንያት ሹመቱ እንደቀረ ያልታወቀውን፣ ወደ ኡጋንዳም ሄዶ በዚያ የነበረውን ዳዊት መሀሪን ከኡጋንዳ ድረስ አምጥቶ ትውልዱ ጎጃም ነው በሚል መስፈርት ብቻ በእነ ዘመነ ካሤ ጥሪ ተደርጎለት፣ እሱም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ተሳፍሮ ወደ ጎጃም ጫካ ገብቶ የዐማራ ፋኖ በጎጃምን የፖለቲካውን ዘርፍ ሰጥተውት እንዲመራ አደረጉት። ለዚህ ነው ዋነኛውን የፋኖ ቁልፍ የፖለቲካ ሥልጣን የያዘው ፓስተር ዳዊት መሀሪ "የፋኖ አንድነት አሁን መምጣት ያለበትም። ሁሉም በየራሱ ጠንካራ ሲሆን እንጂ በዚህ ሁኔታ ወደ አንድ ከመጣን እንፈረካከሳለን፣ ስለዚህ ጎጃም ብቻው መቀጠል አለበት በሚል ገዳይ ምክንያት የዐማራ ፋኖ በጎጃምን እንዲተን፣ እንዲጠፋ እያደረገ ያለው። ፓስተር ዳዊት ወደ አንድ እንምጣ ከተባለም ሁሉንም ሥልጣን ጠቅልለው ለጎጃሞች ይስጡን የሚል መደምደሚያ ይዞ ነው ከአስረስ መዓረይ ጋር እና ከእነ ፓስተር ካሳሁን ጋር ጎጃምን ቀርጥፈው እየበሉ ያሉት።

"…የሚሞተው፣ የሚገደለው፣ የሚታረደው ማነው? በጎጃም አፈር ከደቼ እየበላ ያለ ማነው። ዐማራውና ኦርቶዶክሱ አገው ነው ድራሹ እየጠፋ ያለው። ቅባቶች፣ ፕሮቴስታንቶችና ሸንጎዎች፣ ስኳዶችም ጭምር የዐማራ ፋኖ በጎጃምን ስለተቆጣጠሩት በጎጃም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቄስ፣ ዲያቆን፣ መሪጌታ፣ ሰንበት ተማሪ፣ የቆሎ ተማሪዎች በሙሉ ያለ ርህራሄ ይረሸናሉ። አመራሩ በፆም ሥጋ የሚበላው ጴንጤ ስለሆነ ነው። ይመራል ግን እውነቱን ዋጡት። ባለማዕተብ የጎጃም ዐማራ ፋኖዎች በሙሉ በድሮን እየተለቀሙ እየተገደሉ ነበር እስከቅርብ ጊዜ ጉዳዩን እኔ ይፋ እስከማወጣው ድረስ። ከዚያ በኋላ ቀርቷል በድሮን መገደል። ከጀርባ የሚመቱት የትየለሌ ናቸው። ከኢንጂባራና ከደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ በሚሰጥ መመሪያና ትእዛዝ ምክንያት የጎጃም ኦርቶዶክሱ እየነደደ፣ እያረረ፣ እየወደመ፣ እየታረደም ነው ያለው። የመረጃ ቴሌቭዥኑ አቶ ግርማ ካሣ ሸዋና ጎንደር መከታውና ጌታአስራደ ወደ አንድነት ሳይመጡ ጎጃም ወደ አንድነቱ መግባት የለበትም። ደግ አደረጉ ብሎ የሚደነፋው ሴራው ሌላ ስለሆነ ነው። እኔን በግልፅ ጎጃምን ከነካህ እጣላሃለሁ ሲለኝ የነበረውም ለዚህ ነው። መረጃ ቲቪም እንዲጨልም፣ የሕዝብ ድምጽ ሆኖ እንዳይቀጥል ሳንካ…👇③✍✍✍

19 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.